የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የመደመር መንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ቴክኖሎጂን እንደ ቁልፍ መሣሪያ በመጠቀም እመርታዊ ለውጦችን እያመጣ ይገኛል

Aug 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ቴክኖሎጂን እንደ ቁልፍ መሣሪያ በመጠቀም እመርታዊ ለውጦችን እያመጣ መሆኑን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮናስ አለማየሁ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የተጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ይገኛል።

ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራርን በአንድ ቦታ ላይ በማቅረብ፣ዜጎች የሚፈልጓቸውን አገልግሎቶች በአንድ ቦታ ፈጣን፣ጥራት ያለውና ምቹ በሆነ ሁኔታ እንዲያገኙ አድርጓል።

ይህም የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ከማሳለጡ ባለፈ፣ አጠቃላይ አሰራሩን ግልጽ በማድረግ ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ሁኔታ መከላከል ችሏል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የመንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥ በሂደት መቀየርና መሻሻል የሚገባው ትልቅ ክፍተት በመሆኑ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መቋቋሙን ገልጸዋል።

አገልግሎቶቹን ዲጂታላይዝድ ከማድረግ ባሻገር ተበታትነው የሚገኙ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የተሳለጠ እና ውጤታማ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

ማዕከሉ የተበታተኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን አቀናጅቶ ለዜጎች በአንድ ማዕከል መስጠት ሲሆን ይህም ስኬታማ ነበር ብለዋል።

አገልግሎቶቹን በማቀናጀት ብቻ ሳይወሰን ለዜጎች የሚሰጠው አገልግሎት እርካታን የሚያመጣ እንዲሆን ማድረግ ሌላው የማዕከሉ ዋና ዓላማ መሆኑን ጠቅሰው፥ በዚህ ረገድም ውጤታማ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በአገር አቀፍ ደረጃ ከ110 በላይ ማዕከላት መድረሱንና እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ተገልጋዮች አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት በፍጥነትና በቅልጥፍና ለማሟላት የተለያዩ የአገልግሎት ሞዳሊቲዎችን ተግባራዊ እያደረገ እንዳለም ገልጸዋል።

በአካል ወደ ማዕከሉ መምጣት የማይችሉ ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ የሞባይልና የተንቀሳቃሽ አገልግሎት መጀመሩን ጠቁመዋል።

በዚህም በፌደራል ደረጃ ሁለት እና በአዲስ አበባ ከተማ አንድ በድምሩ ሦስት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎቶች ሥራ መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪ የኦንላይን አገልግሎትና የአፕሊኬሽን ሞዳሊቲዎችን በመጠቀም አገልግሎቶችን እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026