የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚጠይቀውን የዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ትውልድ ማፍራት እያስቻለ ነው - አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ

Aug 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በኢትዮ-ኮደርስ የአምስት ሚሊየን ስልጠና መርሃ ግብር በዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የበለፀገ የሰው ሃይል ለማፍራት በትኩረት እንደሚሰራ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በየደረጃው ባሉ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት እየተደረገበት ነው።


የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ባለፉት አምስት ዓመት በስትራቴጂክ ዕቅድ የመፈጸም ቁርጠኝነታቸውን በቀጣዮቹ ዓመታትም አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የወጣቶችን ተሳትፎና ፈጠራ ማበረታታት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው።

ባለፉት አምስት ዓመታትም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የመዲናዋ ዜጎችን የሥራ ዕድል በመፍጠር የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደተቻለ ገልጸዋል።

በዚህም የአዲስ አበባ ወጣቶች በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን፣ አገልግሎትናበሌሎች ዘርፎች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

በቀጣይም የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አጫጭርና መካከለኛ ሥልጠና በመስጠት ለኢንተርፕራይዞች በቂ የገንዘብ ብድር አቅርቦት እንደሚመቻች አስረድተዋል።

የአዲስ አበባን የዓለም የዲፕሎማሲ ከተማነት የሚመጥንና ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ልህቀት የታጠቀ ወጣት የሰው ሃይል ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮ-ኮደርስ የአምስት ሚሊዮን ስልጠና መርሃ ግብር ይፋ በተደረገ ማግስት ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ወጣቶች የሥልጠናው ተካፋይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታትም ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የመዲናዋ ዜጎች ስልጠና በመስጠት በየትኛውም የዓለም ጫፍ የበይነ መረብ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

በዚህም የ21ኛው ክፍለ ዘመን የቴክኖሎጂና ዲጂታል ሥምሪት የሚጠይቀውን ዕውቀትና ክህሎት የተላበሰ ወጣት ለማፍራት የኮደርስ ሥልጠና ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ደሳለኝ ተረፈ በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ አንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በተቋቋመ ማግስት የተገልጋዮችን እርካታ ከ99 በመቶ በላይ ማድረስ አስችሏል ብለዋል።

በመዲናዋ በ11 ማዕከላት 25 የአዲስ አበባና የፌዴራል ተቋማት 150 አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸው፤ እስከ መስከረም ወር ተጨማሪ ማዕከላት ይገነባሉ ብለዋል።

በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የአገልግሎት አሰጣጡን ከእርካታ ወደ አመኔታ የማሸጋገር ዕቅድ መያዙን በማንሳት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን በተለያዩ አማራጮች እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026