የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምዕራብ ጎንደር ዞን በሰብል ዝርያዎች ምርምርና በመነሻ ዘር ብዜት በትኩረት እየተሰራ ነው

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መተማ፣ ነሐሴ27/2018 (ኢዜአ):- በምዕራብ ጎንደር ዞን የግብርና ምርትና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ በሰብል ዝርያዎች ምርምርና በመነሻ ዘር ብዜት ተግባራት ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል አስታወቀ።

ማዕከሉ እያካሔደ ባለው የዘር ብዜትና ማላመድ ስራ ላይ ያተኮረ የጉብኝት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

በማዕከሉ የቅባትና ጭረት ሰብሎች ምርምር ባለሙያ አቶ እንዳልካቸው አክሊሉ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ማዕከሉ የደጋ፣ ወይና ደጋና ቆላማ አካባቢዎች የሰብል ምርታማነት ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል።

የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ለማውጣት፣ ለማላመድ ፣ ለሰብል አያያዝና ጥበቃ ላይ ያተኮሩ የምርምር ስራዎችን በማከናወን ምርታማነትን በማሳደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዚህም በያዝነው ክረምት በምዕራብ ጎንደር ቆላማ አካባቢዎች በ100 ሄክታር መሬት ላይ 17 የሰብል አይነቶች የዘር ብዜት እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።


ከሁለት ሺህ ኩንታል በላይ ዘር ለዘር አባዥ አርሶ አደሮችና ተቋማት በመስጠት የዘር ብዜትና የማላመድ ተግባሩን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በዚህም በቅርቡ ምርታማነታቸው ተረጋግጦ ይፋ የተደረጉትን "መልካም" የማሽላ፣ "ጠረፍ ወርቅ" የአኩሪ አተር፣ "ማርዘነብ" የሰሊጥና "ጃንተከል" የጥጥ ዝርያን ወደ አርሶ አደሩ ለማድረስ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በማዕከሉ የማሽላ፣ ሰሊጥ ፣ አኩሪ አተር፣ የፈረንጅ ሱፍ ፣ ለውዝ ፣ ጤፍና በቆሎ የመነሻ ዘር ብዜት ስራዎች እያካሄደ መሆኑን ጠቁመው፤ ጉብኝቱም የጀመረውን ተግባር ለማስፋት የሚያስችል ነው።

በማዕከሉ የሩዝ ሰብል ምርምር ባለሙያ አቶ አሳየ ብርሃኑ እንዳሉት፤ የሩዝ ሰብልን ከፎገራና አካባቢው ባሻገር በምዕራብ ጎንደር ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ስጦታ በመጠቀም ለማስፋት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ምርታማነታቸው የተሻሻሉ "ሚሪካ4" እና "አዝመራ" የተሰኙ የሰሊጥ ዝርያዎችን ማቅረባቸውን ጠቁመው፤ አሁን በሄክታር እስከ 60 ኩንታል የሚሰጥ "ፎገራ1" የተሰኘ ዘር እያባዙ መሆኑን ተናግረዋል።

የዛሬው ጉብኝትም በዞኑ በሰፋፊ እርሻ ቦታዎች ሩዝን ለማልማት የሚያስችል እየተደረገ ያለውን ጥረት አመራሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገንዝበው እንዲደግፉ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።

የመተማ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት ፈቃዱ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት በምርጥ ዘር ብዜትና አዳዲስ ዝርያዎችን በማስተዋወቅ ምርታማነት ለማሳደግ ጥረት አድርጓል ነው ያሉት።

በተለይም በምርምር የተገኘውን "መልካም" የተሰኘ የማሽላ ምርጥ ዘር በማቅረብ ቀደም ሲል በሄክታር ከ16 ኩንታል የነበረውን ምርታማነት ወደ 40 ኩንታል እንዲያድግ ማስቻሉን አውስተዋል።

ወረዳውም ማዕከሉ የምርምር ስራውን ለማስፋፋት እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ለወጭ ንግድና ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን ምርት ለማምረት የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በመስክ ጉብኝቱ የተሳተፉት አቶ መስፍን አበራ በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ እያደረገ ያለው የዘር ብዜትና የማላመድ ተግባር በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችና ባለሃብቶችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

"በማዕከሉ ድጋፍ እየተባዛ ያለው ሰብል ቁመና እጅግ አስደሳች ነው" ያሉት አቶ መስፍን፤ ይህም የምርምር ስራው ውጤታማነትን ያረጋገጠ መሆኑን መመልከታቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026