የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጋምቤላ ክልል የእንስሳት ጤና አጠባበቅና ዝርያን በማሻሻል ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር ውጤት አስገኝቷል

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፣ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል የእንስሳት ጤናን በመጠበቅና ዝርያን በማሻሻል ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን የክልሉ ዓሣና እንስሳት ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ25 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሊትር በላይ የወተት ምርት መገኘቱን ቢሮው ገልጿል።

የክልሉ እንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ክርሚስ ሌሮ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በጋምቤላ ክልል ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርታማነት ለማሳደግ የተሻሻሉ ዝርያዎችን የማስራጨትና የእንስሳት ጤና ላይ እየተሰራ ነው።

ይህም ውጤት ማስገኘቱን ገልጸው፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የእንስሳት ሀብት ልማቱን ከሌማት ቱሩፋት መርሃ ግብር ጋር በማስተሳሰር የተሰራው ሥራም ለውጤቱ አስተዋጾ ማድረጉን ተናግረዋል።

ለእዚህም በ2018 በጀት ዓመት 25 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሊትር ወተት፣ ከ12 ሚሊዮን በላይ እንቁላል እና ሌሎች የእንስሳት ተዋጾ ምርት መገኘቱን ጠቅሰዋል።

ቢሮው የእንስሳትን ጤና ለማስጠበቅም ዘመናዊ ላቦራቶሪ የማደራጀትና የእንስሳት ጤና ኬላዎችን ተደራሽ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል።

በተለይም በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ በሰው ሰራሽ ማዳቀል የተጀመሩትን የወተት ላሞች ዝርያ የማሻሻል ሥራዎች በአዲሱ በጀት ዓመትም ወደ ሌሎች ወረዳዎች የማስፋት እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል።

የተሻሻሉ የእንቁላልና የሥጋ ዶሮዎችን በዘርፉ ልማት ለተሰማሩ አርቢዎች ተደራሽ በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የእንስሳት ሀብት ልማቱን ከሌማት ቱሩፋት ኢንሼቲቩ ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የባለሃብቱ፣ የአርሶ እና የአርብቶ አደሩ የዘርፉ ተጠቃሚነት ማደጉን ጠቅሰዋል።

ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ከማሳደጉ ባለፈ በከተሞች የዋጋ ንረትን ለማርገብ እያገዘ መሆኑን ጠቁመዋል።

በክልሉ ማጃንግ ዞን ጎዴሬ ወረዳ በተሻሻሉ የወተት ላሞች እርባታ ሥራ የተሰማረው አቶ ቢተውልኝ ግርማ እንዳሉት የተሻሻሉ የወተት ላሞችን በማርባት ወተትና የወተት ተዋጾን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት ሥራውን በማስፋት በቀን ከ60 ሊትር በላይ ወተት ለህብረተሰቡ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዶሮ እርባታ ሥራ በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የክንድዬና ጓድኞቹ የዶሮ እርባታ ማህበር ተወካይ አቶ ክንድዬ ጥጋቡ ናቸው።

ማህበሩ የእንቁላልና የሥጋ ደሮዎችን በማርባት በጋምቤላ ከተማና አካባቢው ላሉ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026