የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በባሌ ዞን የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት የተመዘገቡ እመርታዊ ለውጦች ይጠናከራሉ

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አጋርፋ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በባሌ ዞን የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት የተመዘገቡ እመርታዊ ለውጦች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ።

በዞኑ የጳጉሜን-1 "የእመርታ ቀን"ን በማስመልከት "እመርታ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የግብርና ልማት ሥራዎች የመስክ ምልከታ በአጋርፋ ወረዳ ተካሂዷል።


በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተሰሩት ሥራዎች እመርታዊ ለውጦች መታየታቸውም ተመልክቷል።

በመርሃግብሩ ላይ የባሌ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አልይ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በዞኑ ከተረጂነት ለመውጣትና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ተግባራዊ የተደረጉ ኢንሼቲቮች ውጤት እያስመዘገቡ ነው።

በተለይ የኩታገጠም አሰራር፣ ምርጥ ዘር አጠቃቀምና ሌሎች የተሻሻሉ አሰራሮች በስፋት እየተተገበሩ መምጣት የእመርታዊ ለውጡ ማሳያዎች መሆናቸውን አክለዋል።


አቶ አልይ እንዳሉት በዞኑ በ2018/2019 የምርት ዘመን ከ580 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ አፍራሳ እንዳሉት በዞኑ ባለፉት ዓመታት የግብርና ሜካናይዜሽን በማስፋፋት የተመዘገቡ እመርታዊ ለውጦች ይጠናከራሉ።


በተለይ የኩታገጠም አሰራርን ማስፋት፣ የሰብል ምርትን ማሳደግ፣ የበጋ መስኖን ልማትን ማጠናከርና ዘመናዊ የእንስሳት እርባታን ማስፋፋት አበረታች ውጤት ማምጣቱን ገልጸዋል።

በዞኑ ባለፉት ዓመታት የግብርና ሜካናይዜሽንና ዘመናዊ የግብርና አሰራርን በማስፋፋት የተመዘገቡ እመርታዊ ለውጦች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አቶ ብርሀኑ አስታውቀዋል።

የአጋርፋ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አደም ከድር በሰጡት አስተያየት በ 2 ሄክታር መሬታቸው ላይ በኩታገጠም እያለሙ ካለው የስንዴ ልማት የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026