የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ለዘመን መለወጫ የእርድ እንስሳት እና የበዓል ፍጆታ ቁሶች በበቂ ሁኔታ ቀርበዋል

Sep 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጉደር፤ ጳጉሜን 3/2018(ኢዜአ)፡- ለዘመን መለወጫ የበዓል ገበያ የእርድ እንስሳት እና የተለያዩ የበዓል ፍጆታ ምርቶች አቅርቦት በቂ መሆኑን በምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ ነጋዴዎችና ሸማቾች አስታወቁ።

የዘመን መለወጫ በዓል ሲቃረብ በየአካባቢው የሚከፈቱ የበዓል ገበያዎች ከፍተኛ የህዝብ እንቅስቃሴና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚታይባቸው ናቸው።


በተለይም የገበያውን ፍላጎትና አቅርቦት ለማጣጣም ከተለያዩ ክልሎች ወደ ዋና ዋና ከተሞች የሚገቡ የእርድ እንስሳት እንዲሁም የመሠረታዊ ምግብ ነክ ቁሶች ስርጭት የተሻለ እንዲሆን በሁሉም አካላት ጥረት ተደርጓል።

የአቅርቦቱ ማደግ ደግሞ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪን በመግታት ህብረተሰቡ እንደየምርጫውና እንደአቅሙ ገበያ ወጥቶ እንዲሸምት መንገድ አመቻችቷል።


ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉደር ከተማ ነጋዴዎችና ሸማቾች፤ ለአዲሱ ዓመት በዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት እና የተለያዩ የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ለገበያ በመቅረባቸው፣ ህብረተሰቡ እንደየአቅሙ እየተገበያየ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በከተማው የቁም እንስሳት ገበያ ከተገኙት ሸማቾች መካከል አቶ ንጉሴ ከፈኒ፤ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ አቅርቦትና የተረጋጋ ግብይት መኖሩን ገልጸዋል።

የዘንድሮው የአዲሱ ዓመት የበዓል ገበያ ዋጋ ተመጣጣኝ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንደየአቅሙ እየተገበያየ እንደሚገኝ በመጥቀስ፤ የምርቶች አቅርቦትም በስፋት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ሌላው አስተያየት ሰጪ ነጋዴ አቶ አሰፋ ሽብሩ በበኩላቸው፤ የእርድ እንስሳት አቅርቦቱ በቂ ቢሆንም መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መኖሩን ጠቁመው፣ በገበያው ከፍተኛው የሰባ በሬ እስከ 150 ሺህ ብር እየተሸጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዓሉ የደስታና የመረዳዳት እንዲሆንም ያላቸው ከሌላቸው ጋር በመቋደስ ማሳለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የበዓሉ ገበያ የተረጋጋ መሆኑንና የአትክልትና ፍራፍሬ አቅርቦት በብዛትና በጥራት መኖሩን የገለፁት ወይዘሮ አስካለች አለሙ ናቸው፡፡


በተጨማሪም አላስፈላጊ የዋጋ ንረት እንዳይኖር የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው፣ እስካሁን ጥሩ የግብይት እንቅስቃሴ መኖሩን ገልጸዋል።

የምዕራብ ሸዋ ዞን ንግድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ አቶ ተሰማ ኩምሳ፤ ለበዓሉ ከዞን እስከ ቀበሌ የሚደርስ ኮሚቴ በማደራጀት ህብረተሰቡ የበዓል ፍጆታ ምርቶችንና የእርድ እንስሳትን ያለ አቅርቦት እጥረት እንዲያገኝ መደረጉን ገልጸዋል።

በግብይት ሂደቱ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ከተስተዋሉ ህብረተሰቡ ጥቆማ መስጠት እንደሚችል ያነሱት ተወካዩ፣ በሁሉም አካባቢዎች ጥብቅ የቁጥጥርና ክትትል ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

አምራችና ሸማች በቀጥታ የሚገናኙባቸው የገበያ ማዕከላት በመቋቋማቸው ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገበያይ እድል መፈጠሩን ያነሱት ተወካዩ፣ ለአዲሱ ዓመት በዓሉ የዶሮ፣ የበግና የፍየል አቅርቦት በስፋት መኖሩን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026