የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት ስራዎች ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋገጠ

Sep 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት አጀንዳዎች እንደሚደግፍ አስታወቀ።


የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አዲሷን የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።


በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተሳትፈዋል።


የሁለቱ ወገኖች ውይይት ባንኩ በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተሳትፎ ጨምሮ በአበይት የኢትዮጵያ የልማት ትኩረቶች ላይ ያተኮረ ነው።


ከዚህም ባሻገር በኢነርጂ ዘርፍ እና የአየር ንብረት ለውጥን በሚከላከሉ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ያላቸውን አጋርነት ማሳደግ፣ በዝቅተኛ ወለድ የሚሰጡ የብድር አቅርቦቶችን ማመቻቸት እንዲሁም ከሌሎች ባለብዙ ወገን የልማት ባንኮች ጋር በቅንጅት መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል።


በውይይቱ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ለፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ የኢትዮጵያ ሪፎርም አጀንዳ አፈጻጸም እና እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።


ሚኒስትሩ አክለውም ባንኩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጣቸውን የልማት ትኩረቶች መደገፍ የሚችልባቸውን የፋይናንስ አማራጮች አቅርበዋል።


ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው የኃይል ትስስርን በማስፋት ረገድ እየተወጣች ያለውን ግንባር ቀደም ሚና አድንቀዋል።


ባንኩ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት አጀንዳ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል።


ሁለቱ ወገኖች አጋርነታቸውን በማጎልበት፤ ዘላቂና አሳታፊ የመሰረተ ልማት ዕድገትን በጋራ እውን ለማድረግ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።


የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ እንደሚገኝ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026