የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ዜጎችን በዲጂታል ክህሎት በማብቃት የሥራ ዕድልና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ

Sep 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዜጎችን በዲጂታል ክህሎት በማብቃት የሥራ ዕድልና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ።

በክልሉ "የነገ ቀን" የዲጂታል ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት! በሚል መሪ ሀሳብ በክልል ደረጃ በሆሳዕና ከተማ ተከብሯል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት በማሳደግ የተወዳዳሪነት አድማስን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ።

በተለይ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከ310 ሺህ 800 በላይ ዜጎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ከ237 ሺህ በላይ ሰልጣኞችም እውቅናና ምስክር ወረቀት አግኝተዋል ብለዋል።

ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቁ የሆኑና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

አቶ አንተነህ እንደገለጹት በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን 7 መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ተገንብተው ለአገልግሎት በመብቃታቸው የተገልጋይን እንግልት ማስቀረት ተችሏል ብለዋል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ንጉሴ አስረስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን በመተግበር የአገልግሎት ጥራትና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በቴክኖሎጂ የበቃ ትውልድን የመገንባት ስራ አይነተኛ ሚና አለው ነው ያሉት፡፡

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብድልሙህሲን ሀሰን (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት የበለፀገች ሀገርን ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ግንባታ ላይ አተኩሮ መስራት ያስፈልጋል።


ለክልሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር ስኬታማነት ዩኒቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድጋፍ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል።

በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ባገኘው እውቀት በቴክኖሎጂ የታገዘ የፈጠራ ሥራዎችን በማከናወን ተጠቃሚ መሆን እንደጀመረ የተናገረው ደግሞ በመድረኩ የተገኘው ወጣት ሙአዝ በድሩ ነው።

የነገ ቀንን በማስመልከት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ የክልሉ፤ የዞንና የተለያዩ መዋቅሮች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተማሪዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026