የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Sep 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ) ፡- የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ የስንዴ ልማት እሴት ሰንሰለት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ለኢዜአ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የስንዴ ልማት እሴት ሰንሰለት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ የስንዴ ሰብሉ ድርቅን፣ ከፍተኛ ሙቀትን፣ ተባዮችንና ያልተጠበቀ የዝናብ መዛባትን የሚቋቋሙ የምርጥ ዘር ዝርያዎችን መጠቀም ላይ እንደሚያተኩርም ተገልጿል።

በፕሮጀክቱ በስንዴ ልማቱ ላይ የሚካሄዱት የድጋፍና ክትትል ተግባራቱ በምርት ላይ ብቻ የተወሰኑ ሳይሆኑ ሙሉ የልማት የእሴት ሰንሰለቱን የሚያካትት መሆኑም እንዲሁ።

ይህ አሰራር ለገበሬዎች ከዘርና ቴክኖሎጂ አቅርቦት ጀምሮ እስከ ሰብል ስብሰባ፣ ማከማቸት፣ ማቀናበርና ምርቱን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ እስከ ማቅረብ ያሉትን ሙሉ ሂደቶች ያቃልላል ተብሏል።

በአጠቃላይ ሀገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ በሚያመጣው ተጽዕኖ ሳትበገር የስንዴ ምርቷን በማሳደግ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥና ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማጠናከር እያደረገች ያለችውን የተቀናጀ እንቅስቃሴ የሚደግፍ ፕሮጀክት መሆኑ ነው የተገለጸው።

በግብርና ሚኒስቴር የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ አብዱልሰመድ አብዶ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ ሶማሌ እና አፋር ክልሎች ነው።

በዚህም በክልሎቹ የሚገኙ 76 ወረዳዎችና 1 ሺህ 129 ቀበሌዎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

ለአምስት አመታት ተግባራዊ በሚደረገው በዚህ ፕሮጀክት በአካባቢዎቹ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል አነስተኛ ይዞታ ያላቸው ስንዴ አምራች አርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።

በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል የዘር ግብዓት አቅርቦት ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም በየደረጃው ከሚገኙ የግብርና ምርምር ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በተደረገባቸው ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የዳቦና የመኮሮኒ ስንዴ ዘርን በጥራት በማምረት በፕሮጀክቱ ለታቀፉ አርሶ አደሮች ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል።

ይህም የመነሻ ዘር አቅርቦት ከማሻሻል ባለፈ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ማስቻሉን አመላክተዋል።

ፕሮጀክቱ ከአፈር ለምነትና ጤንነት ጋር ተያይዞ ስንዴ አምራች በሆኑ አካባቢዎች እያጋጠመ ያለውን ሰፊ የአሲዳማነት ችግርንም ለማቃለል ትኩረት መስጠቱን አስተባባሪው አስታውቀዋል።

በዚህ ረገድ ስለ ኖራ አጠቃቀም ለአርሶ አደሩ በሰርቶ ማሳያ በማሳየት በአሲዳማነት የተጠቃ አፈርን በማከም ምርታማነት እንዲሻሻል በፕሮጀክቱ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የኖራ አቅርቦትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ትላልቅ የኖራ ወፍጮዎች እየተተከሉ ሲሆን፣ ለአፈር ለምነት የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ ስራም ተያይዞ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ለመስኖ ልማት አመቺ በሆኑ አካባቢዎች የ18 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ የጠቆሙት ኃላፊው፣ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሜካናይዜሽን ማዕከላትን ከመገንባት ጎን ለጎን በአራቱ ክልሎች 49 ትላልቅና መካከለኛ የስንዴ ማከማቻ መጋዘኖችን የመገንባት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 94 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ይህ ፕሮጀክት፣ መንግሥት የስንዴን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ለያዘው ስትራቴጂ ስኬታማነት ወሳኝ ድርሻ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026