የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የሕልውና ጥያቄ ነው

Sep 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን ጠንካራ መሰረት ያለው የሕልውና ጥያቄ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ ገለጹ።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን በሴራ ማጣት በትራንስፖርት፣ በሎጂስቲክስና በወደብ አገልግሎት የገቢና ወጪ ንግድ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያደረሰ ይገኛል።

በየዓመቱም በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ እንድትከፍል በማስገደድ በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገትና እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያስከተለ ነው።

ይህም የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት የሀገርን ተፈጥሯዊ፣ መልክዓ ምድራዊ፣ ስትራቴጂካዊና ሕጋዊ የባሕር በር ባለቤትነት ለማስመለስ ያነሱትን ጥያቄ ምክንያታዊነት ያጎላዋል።

ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በባሕር ላይ የሎጂስቲክስና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት ጠንካራ አቅም የገነባች ሀገር ናት።

በባሕር ላይ የንግድ መስመር፣ የሎጂስቲክስና ትራንስፖርት እንቅስቃሴም በትላልቅ መርከቦች፣ ብቁ የመርከብ ካፒቴኖችና በዳበረ መዋቅር የሚከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያን አቅም የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣት የሚያስቆጭ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ይህም በባሕር ላይ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እንዳለው አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለሺህ ዘመናት ስትጠቀምባቸው ከነበሩት የቀይ ባሕር ሉዓላዊ ወደቦቿ እንድትገለል የተፈጸመባት ታሪክ ይቅር የማይለው በደል በዘርፉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያሳደረባት መሆኑን ገልጸዋል።

የባሕር በር አለመኖሩም ኢትዮጵያን በወደብ ኪራይ፣ በሸቀጦች የወጪና ገቢ እንቅስቃሴ መዘገየት በመፍጠርና ቀጥተኛ ተፅዕኖ በማሳደር የኢኮኖሚ ዕድገትን እየጎተተ መሆኑን አስረድተዋል።

የባሕር በር ባለቤትነትም በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የወደብ አገልግሎት የሚያጋጥሙ ተፅዕኖዎችን በማስቀረትና የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ለዜጎች የሕይወት መሻሻል መሠረት መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም በወደብ አገልግሎት የሚያጋጥሙ የትራንዚት መጨናነቅን፣ የገቢና ወጪ ምርት መዘግየትንና የወደብ ኪራይን ለማስቀረት ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የኢትዮጵያን ታሪካዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የህልውና ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል።

የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው ጥረትም ሁሉም ዜጋ በትብብርና በንቁ ተሳትፎ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026