የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ9ኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመባል ተሸለመ

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2019 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2026 የስካይትራክስ የዓለም አየር መንገድ ሽልማት ለዘጠኝ ተከታታይ ዓመት በአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመባል ሽልማትን አግኝቷል።

አየር መንገዱ በአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክላስ እና በአፍሪካ ምርጥ የኢኮኖሚ ክላስ አገልግሎት ሽልማቶችንም ተቀብሏል።

የአፍሪካ ቀዳሚው አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2026 የSKYTRAX የዓለም አየር መንገድ ሽልማቶች ላይ ለዘጠኝ ተከታታይ ዓመት በመመረጥ የአህጉሪቱ ቁጥር አንድ አየር መንገድነቱን አረጋግጧል።

ከዚህ ታላቅ እውቅና በተጨማሪ አየር መንገዱ በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎችም ሽልማቶችን አግኝቷል። ሽልማቶቹም በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ አየር መንገድ፣ በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ የኢኮኖሚ ክላስ አገልግሎት አሰጣጥ እና በአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክላስ የሚሉት ናቸው፡፡

ሽልማቶቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለጥራት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደንበኞች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ያላቸውን እምነትና ታማኝነት ያንፀባርቃሉ።

ዕውቅናው አየር መንገዱ የላቀ አገልግሎት ለመስጠት፣ ልዩ የደንበኞችን እርካታ ለመጠበቅ እና በዓለም አቀፍ አውታረ መረቡ ውስጥ እንከን የለሽ የጉዞ ልምድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ነው።

በተጨማሪም የአየር መንገዱን ሰራተኞች ያላሰለሰ ጥረት የሚያጎላ ሲሆን፣ በአፍሪካ ግንባር ቀደም የአቪዬሽን ቡድን መሆኑን ያረጋግጣል።

ሽልማቶቹ አየር መንገዱ የአገልግሎቶች እና የአሠራሮች ደረጃ በመጠበቅ ረገድ ያለውን ቁርጠኛነት የሚያረጋግጥ መሆኑን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026