የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት በማደግ ላይ የሚገኙ አገራትን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ እንዲሰሩ  የማሻሻያ ስራዎች ተጀምረዋል - አንቶኒዮ ጉተሬዝ 

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 30/2016 (ኢዜአ)፡- የመንግስታቱ ድርጅት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት በማደግ ላይ የሚገኙ አገራትን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ እንዲሰሩ የማሻሻያ ስራዎች መጀመሩን የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ50 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የታደሙበት የቻይና-አፍሪካ የትብብር ጉባዔ ትናንት በቤጂንግ ተከፍቷል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የቻይናን ያልተቋረጠ ድጋፍ ታደንቃለች ብለዋል።

በጉባኤው ላይ የተገኙት የተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከሲጂቲኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ አፍሪካ የቅኝ አገዛዝ ድርብ ተጠቂ መሆኗን ጠቅሰው ጉዳቱ የሚጀምረው ራሱ የቅኝ አገዛዝ ካደረሰባት ጫና መሆኑን አስታውቀዋል።

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ያደረሱባት የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ሌላው ጫና መሆኑን ተናግረዋል።

የቅኝ አገዛዙ ድርብ ጫና በፈጠረባቸው ፈተና በርካታ የአፍሪካ አገራት ህልውናቸውን በራሳቸው አቅም ማስቀጥል የማይችሉ እንደነበሩ ገልጸዋል።

በዚህም አፍሪካ በዓለም አደባባይ በበቂ ሁኔታ መወከል አለመቻሏን በማንሳት ተግባሩን ነጥለን ካየነው በተለይም አህጉሪቱ በኢኮኖሚና በፋይናንስ ዘርፍ የደረሰባት መገለል በጣም አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት በማደግ ላይ የሚገኙ አገራትን ፍላጎት በበቂ ሁኔታ ለመሸፈን አለመፈለጋቸውና አገራቱ በተቋማቱ ውስጥ በሚፈለገው ልክ አለመወከላቸው ችግሩን አባብሶታል ብለዋል።

ይሀንን ችግር ለመፍታት የመንግስታቱ ድርጅት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማትን አሰራር ለማሻሻል ስራዎች መጀመሩን ጠቅሰዋል።

ማሻሻያው በማደግ ላይ የሚገኙ አገራትን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ እንዲተገበር እየሰራን ነው ብለዋል።

ቻይና ዘላቂነት ያለውን የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካትና የራሷን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ አገራትን ፍላጎት ለሟሟላት ከፍተኛ ኃላፊነት ወስዳ እየሰራች መሆኑን ዋና ፀሐፊው አስረድተዋል።

የቻይና አፍሪካ ግንኙነት የደቡብ-ደቡብ ትብብርን የሚያንጸባርቅ መሆኑን በመጥቀስ ቻይና አፍሪካ የምትፈልገውን ኢንቨስትመንት በማቅረብ በኩል የሚጠበቅባትን ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።

አፍሪካ በመሰረተ ልማት፣ ትምህርትና ጤና ዘርፍ ያሉባትን ጉድለቶች ለመሙላት በምታደርገው ጥረት የቻይና እገዛ ከፍተኛ ቦታ ይይዛል ብለዋል።

ቻይና ለአፍሪካ አገራት እያደረገች ያለው እገዛ ትልቅ እድል ይዞ መምጣቱን የተናገሩት ዋና ፀሐፊው አጀንዳ 2030ን ለማሳካት የቻይና አስተዋጽኦ ከፍተኛ ቦታ እንዳለው ተናግረዋል።

ዘላቂነት ያለውን የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትን ማሻሻል ዋነኛው እርምጃ መሆኑን አስታውቀዋል።

ለሦስት ቀናት በሚካሔደው የቻይና-አፍሪካ የትብብር ጉባዔ እአአ እስከ 2027 በሚኖረው የቻይና እና አፍሪካ ግንኙነት የትብብር ሰነዶች ላይ ውይይት ተደርጎ ስምምነት እንደሚፈረም ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025