
አዲስ አበባ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቋቋም የሚያስችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እያከናወነች መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም “ከእመርታ ወደ ብልጽግና፤ የአፍሪካን ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች አቅም ማጠናከር” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የቢዝነስ ፎረሙ በአፍሪካ የቁም እንስሳት፣ ግብርና እና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎች ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለት እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ልማት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በምርቶች ላይ እሴት መጨመር የአፍሪካን ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ያሳድጋል።
ለኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ስራ ዕድል ፈጠራ ያለውን ፋይዳም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን ከማሳደግ ረገድ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዘግቧን ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ምርታማነትን በመጨመር በስንዴ ምርት ራሷን መቻሏን ጠቁመዋል።
በአፍሪካ የማምረት አቅምን ለማሳደግ ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባም ገልጸዋል።
በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ለኢንቨስትመነት ፍሰት ምቹ ሁኔታ መፍጠሯን አንስተዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026