የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለወጪ ንግድ እድገት ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው-ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዝያ 6/2017 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው ለወጪ ንግድ እድገት ጉልህ ሚና ማበርከቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀን አፈጻጸም እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ በሀገሪቱ የንግድ ካባቢ ተወዳዳሪ መሆን የሚችልበትን አቅም የመፍጠር እና የተቀላጠፈ አሰራርን የመዘርጋት ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች አዲስ የንግድ ፈቃድና የዕድሳት አገልግሎት መሰጠቱንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ600 ሺህ ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

በድህረ ፈቃድ ክትትልና ቁጥጥር 250 ሺህ ነጋዴዎች የንግድ ፈቃዳቸውን ከህግ አግባብ ውጭ እየተጠቀሙበት በመገኘታቸው ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ነው ያሉት።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተመዘገበው የወጪ ንግድ ገቢ በታሪክ ከፍተኛው መሆኑን በማንሳት፥ ለዚህም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ትልቅ አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል።

የምርት አቅርቦትንና ጥራትን በማሻሻል እንዲሁም የግብይት ተደራሽነትን በማስፋት የኑሮ ውድነትን ማረጋጋትና የንግዱን ዘርፍ ተወዳዳሪነት ማሳደግ ላይ አመርቂ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።

የገቢና ወጪ ምርቶች ላይ ክትትልና ቁጥጥር የማድረግ አቅም 39 በመቶ እድገት ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገው ድርድር ግብ እንዲመታ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል።

በቀጣይ ሦስት ወራት ወጪ ንግድን ማሳደግ፣ ዲጅታላይዜሽንን ማፋጠን፣ የኢ-ኮሜርስ ስራን ተቋማዊ ማድረግ፣ የጥራት ቁጥጥርን ማጠናከር እና የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣናን ወደ ሙከራ ትግበራ ማስገባት ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026