የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂና የምርምር ሥራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል

May 6, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ሚያዚያ 22/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የቴክኖሎጂና ምርምር ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባቸው ተገለፀ።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ''ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ቃል የክህሎት፣የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደ ርዕይ በቦንጋ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በክልሉ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በቴክኖሎጂና ምርምር ዘርፍ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ሥራዎችን ማፍለቅ ይጠበቅባቸዋል።

ይህን እውን ለማድረግም ለተቋማቱ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ።

ተቋማቱ በስነምግባር የታነፀ የፈጠራ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል በማፍራትና ዘርፉ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያደርግበትን አቅም መፍጠር ላይ ተጨማሪ ስራ መስራት እንደሚጠይቅም አመልክተዋል።

የቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ተቋማቱ የክልሉን የልማት ጸጋ ማዕከል ያደረገ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን መቅዳት ላይ አተኩረው እንዲሰሩ የሚደረገው ጥረት እንደሚጠናከር የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አብይ አንደሞ ( ዶ/ር) ናቸው።

የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ ከስልጠና በተጨማሪ በምርምር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ቤቴልሔም ዳንኤል በበኩላቸው፥ በክልሉ የሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የክህሎት፣ቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደርዕይ የትምህርት ተቋማቱ በክህሎት፣በቴክኖሎጂና በፈጠራ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት የሚያደርጉትን ጥረትን የሚያግዝ ነው።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆው ውድድር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተሰሩ የተለያዩ የቴክኖሎጂ፣የፈጠራ እና የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን አሸናፊ ለሚሆኑት ማበረታቻ ሽልማትና ዕውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025