የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂና የምርምር ሥራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል

May 6, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ሚያዚያ 22/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የቴክኖሎጂና ምርምር ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባቸው ተገለፀ።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ''ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ቃል የክህሎት፣የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደ ርዕይ በቦንጋ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በክልሉ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በቴክኖሎጂና ምርምር ዘርፍ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ሥራዎችን ማፍለቅ ይጠበቅባቸዋል።

ይህን እውን ለማድረግም ለተቋማቱ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ።

ተቋማቱ በስነምግባር የታነፀ የፈጠራ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል በማፍራትና ዘርፉ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያደርግበትን አቅም መፍጠር ላይ ተጨማሪ ስራ መስራት እንደሚጠይቅም አመልክተዋል።

የቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ተቋማቱ የክልሉን የልማት ጸጋ ማዕከል ያደረገ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን መቅዳት ላይ አተኩረው እንዲሰሩ የሚደረገው ጥረት እንደሚጠናከር የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አብይ አንደሞ ( ዶ/ር) ናቸው።

የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ ከስልጠና በተጨማሪ በምርምር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ቤቴልሔም ዳንኤል በበኩላቸው፥ በክልሉ የሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የክህሎት፣ቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደርዕይ የትምህርት ተቋማቱ በክህሎት፣በቴክኖሎጂና በፈጠራ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት የሚያደርጉትን ጥረትን የሚያግዝ ነው።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆው ውድድር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተሰሩ የተለያዩ የቴክኖሎጂ፣የፈጠራ እና የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን አሸናፊ ለሚሆኑት ማበረታቻ ሽልማትና ዕውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026