የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂና የምርምር ሥራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል

May 6, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ሚያዚያ 22/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የቴክኖሎጂና ምርምር ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባቸው ተገለፀ።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ''ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ቃል የክህሎት፣የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደ ርዕይ በቦንጋ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በክልሉ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በቴክኖሎጂና ምርምር ዘርፍ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ሥራዎችን ማፍለቅ ይጠበቅባቸዋል።

ይህን እውን ለማድረግም ለተቋማቱ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ።

ተቋማቱ በስነምግባር የታነፀ የፈጠራ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል በማፍራትና ዘርፉ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያደርግበትን አቅም መፍጠር ላይ ተጨማሪ ስራ መስራት እንደሚጠይቅም አመልክተዋል።

የቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ተቋማቱ የክልሉን የልማት ጸጋ ማዕከል ያደረገ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን መቅዳት ላይ አተኩረው እንዲሰሩ የሚደረገው ጥረት እንደሚጠናከር የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አብይ አንደሞ ( ዶ/ር) ናቸው።

የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ ከስልጠና በተጨማሪ በምርምር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ቤቴልሔም ዳንኤል በበኩላቸው፥ በክልሉ የሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የክህሎት፣ቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደርዕይ የትምህርት ተቋማቱ በክህሎት፣በቴክኖሎጂና በፈጠራ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት የሚያደርጉትን ጥረትን የሚያግዝ ነው።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆው ውድድር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተሰሩ የተለያዩ የቴክኖሎጂ፣የፈጠራ እና የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን አሸናፊ ለሚሆኑት ማበረታቻ ሽልማትና ዕውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026