
ሆሳዕና፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄና የልማት ፍላጎት በአግባቡ በመገንዘብ ምላሽ መስጠት የሚችል አመራር የመፍጠር ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ የክልሉ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።

በዚሁ መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤በዚህ ዘመን ወቅቱን የዋጀና የህዝቡን ፋላጎት በአግባቡ በመረዳት ሌት ተቀን መስራት የሚችል አመራር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጣን መፍትሄ የሚሰጥ በእቅድ የሚመራ እና ህዝብን በቅንነት የሚያገለግል ብቁና ጠንካራ አመራር መፍጠር ይገባል ብለዋል።
የመድረኩም ዓላማ ይህንኑ መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ እውነተኛ የህዝብ አገልጋይ ለመሆን ራሱን እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
በሀገሪቷ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሁሉም መስኮች አስደናቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተው፥ የተቀመጠውን የብልጽግና መዳረሻ ለማሳካት ከመቼውም ጊዜ በላይ የአመራሩ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል።
በየደረጃው ያለው አመራር የህዝብን አቅም በማስተባበር ክልሉን ብሎም ሀገርን የሚለውጡ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026