
ሆሳዕና፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄና የልማት ፍላጎት በአግባቡ በመገንዘብ ምላሽ መስጠት የሚችል አመራር የመፍጠር ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ የክልሉ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።

በዚሁ መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤በዚህ ዘመን ወቅቱን የዋጀና የህዝቡን ፋላጎት በአግባቡ በመረዳት ሌት ተቀን መስራት የሚችል አመራር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጣን መፍትሄ የሚሰጥ በእቅድ የሚመራ እና ህዝብን በቅንነት የሚያገለግል ብቁና ጠንካራ አመራር መፍጠር ይገባል ብለዋል።
የመድረኩም ዓላማ ይህንኑ መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ እውነተኛ የህዝብ አገልጋይ ለመሆን ራሱን እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
በሀገሪቷ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሁሉም መስኮች አስደናቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተው፥ የተቀመጠውን የብልጽግና መዳረሻ ለማሳካት ከመቼውም ጊዜ በላይ የአመራሩ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል።
በየደረጃው ያለው አመራር የህዝብን አቅም በማስተባበር ክልሉን ብሎም ሀገርን የሚለውጡ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026