
ሆሳዕና፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄና የልማት ፍላጎት በአግባቡ በመገንዘብ ምላሽ መስጠት የሚችል አመራር የመፍጠር ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ የክልሉ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።

በዚሁ መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤በዚህ ዘመን ወቅቱን የዋጀና የህዝቡን ፋላጎት በአግባቡ በመረዳት ሌት ተቀን መስራት የሚችል አመራር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጣን መፍትሄ የሚሰጥ በእቅድ የሚመራ እና ህዝብን በቅንነት የሚያገለግል ብቁና ጠንካራ አመራር መፍጠር ይገባል ብለዋል።
የመድረኩም ዓላማ ይህንኑ መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ እውነተኛ የህዝብ አገልጋይ ለመሆን ራሱን እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
በሀገሪቷ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሁሉም መስኮች አስደናቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተው፥ የተቀመጠውን የብልጽግና መዳረሻ ለማሳካት ከመቼውም ጊዜ በላይ የአመራሩ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል።
በየደረጃው ያለው አመራር የህዝብን አቅም በማስተባበር ክልሉን ብሎም ሀገርን የሚለውጡ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026