የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ግብርን በወቅቱ በመክፈል በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን እናስቀጥላለን - የመቱ ከተማ ግብር ከፋዮች

Jul 11, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ ግብርን በወቅቱ በመክፈል በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የመቱ ከተማ ግብር ከፋዮች ተናገሩ።


በከተማው በ2018 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ከ1 ቢሊዮን 100 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን የመቱ ከተማ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ግብር ከፋዮች እንደገለፁት፤ በከተማዋ የተጀመሩ የኮሪደርም ሆነ ሌሎች የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ግብርን በወቅቱ በመክፈል የድርሻችንን እንወጣለን።


ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ስመኢሉ አበበ በከተማው የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋይ ሲሆኑ ግብርን መክፈል የሀገር ልማትን በማረጋገጥ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ወሳኝ ነው።


ለዚህም ግብርን በወቅቱ በመክፈል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።


አቶ ሺፋ ቀኖ የተባሉ ግብር ከፋይ በበኩላቸው ግብርን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል ልማትን መጠየቅ ተገቢ ነው ብለዋል።


ግብርን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን የገለፁት ወይዘሮ ካሰች ገዛኸኝ በከተማዋ እየተከናወነ ባለው የልማት ስራ ከተማዋ እየተለወች መሆኑን ተናግረዋል።


ለዚህም ግብርን በወቅቱ ከመክፈል በተጨማሪ ለከተማዋ ልማት መፋጠን የበኩላቸውን እንደሚወጡ አመልክተዋል።


በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ለታቀደለት ዓላማ ለማዋል በትኩረት ተግተን እየሰራን ነው ያሉት ደግሞ የመቱ ከተማ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዳንኤል ደበበ ናቸው።


በዚህም ባለፈው በጀት ዓመት 700 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ተናግረው በ2018 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ከ1 ቢሊዮን 100 ሚሊዮን በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን አመልክተዋል።


በከተማው በተያዘው የበጀት ዓመት የገቢ ግብር አሰባሰቡን ስኬታማ ለማድረግ ግብር ከፋዮች ያለምንም እንግልትና የጊዜ ብክነት ግብር መክፈል የሚችሉበት የዘመነ የግብር አከፋፈል ስርዓት መዘርጋቱን ገልጸዋል።


የመቱ ከተማ ምክትል ከንቲባ ጆን ተስፋዬ በበኩላቸው በከተማው የሚታቀዱ የልማት ስራዎችን ከግብ ለማድረስ ከሁሉም የገቢ ምንጮች ለመሰብሰብ የታቀደውን ለማሳካት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026