የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች ለሀገር እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል ይፈጥራል - ቋሚ ኮሚቴው

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ቋሚ ኮሚቴው የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የባለድርሻ አካላት አስረጂ መድረክ አካሂዷል።


የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ቤተልሔም ላቀው(ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በቋሚ ኮሜቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በዝርዝር አቅርበዋል።

በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ አንቀጾች ላይ የሚስተዋሉ የግልጽነትና የትርጓሜ ለውጥ የሚያመጡ ሃሳቦች በድጋሚ ሊፈተሹ እንደሚገባ አንስተዋል።

እንዲሁም የረቂቅ አዋጁን የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት፣ የአጋር አካላት ሚና እና የአዋጁን አስፈላጊነት በሚመለከት ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፤ ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በምላሻቸውም ረቂቅ አዋጁ እንደሀገር የሃብት ምንጭ የሆኑ አዳዲስ አማራጮችንና አሰራሮችን ለማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

በዋናነት መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለውን ተግባር ''ከሃሳብ እስከ አምራችነት'' የሚለውን እሳቤ የሚደግፍ መሆኑንም አንስተዋል።

ረቂቅ አዋጁ የወጣቱን አምራችነት ለማሳደግ እንዲያግዝ ታልሞ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም አስቻይ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል ነው ያሉት።

ቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጁን በሚመለከት የሰጠው ግብረ መልስ ጉድለቶችን ለማረምና ለመፈተሽ የሚያግዝ በመሆኑ የቀጣይ የቤት ስራ በማድረግ የመፈተሽ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላትን የማምረት አቅም ለማጉላት እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸው፤ በእውቀትና ፈጠራ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

ረቂቅ አዋጁን ይበልጥ ለማዳበር ስታርታፖችንና ባለድርሻ አካላትን በቅርበት የማወያየትና ግብዓት የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል።


በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በሰጡት ማጠቃለያ፤ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥር አብራርተዋል።

ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ያላትን የወጣት ኃይል በተገቢው መልኩ ለመጠቀምና የፈጠራ ሃሳብ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

የተለያየ የፈጠራ ሃሳብ፣ ችሎታና በቴክኖሎጂ የዳበረ እውቀት ያላቸው ስታርታፖች በመረጡት መስክ ተሰማርተው ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አዋጁ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026