የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ ነው - የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ገለጹ።

ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚያደርግ ተቋም ነው ብለዋል።

በዚህም 52 የትኩረት መስኮችን በመለየት በ14 ዲፓርትመንቶች 6 ማእከሎችን በማዘጋጀት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የምርምር ስራዎቹም በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ማስረጃን መሰረት ያደረጉ የጥናት ውጤቶችንም ለሚመለከታቸው ፖሊሲ አውጪዎች እና አስፈጻሚዎች ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ ምርምሮች መደረጋቸውን ተናግረዋል።

እነዚህ ምርምሮችም ነባር ፖሊሲዎችን የፈተሹ፣ አዳዲስ ፖሊሲዎችን ያመላከቱ እና ፋይዳ ምልከታ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የጥናት መነሻዎቹ እንደ ሀገር የተቀመጡ እቅዶች እና የመንግስት አቅጣጫዎች መሆናቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ፈጣን እደገት ያስመዘገቡ ሀገራት ትልልቅ የምርምር ተቋማት እንዳላቸው አንስተዋል።

እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦች እና ህልሞች እውን እንዲሆኑ በጥናት መደገፍ እንደሚገባ በመግለጽ።

ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የተሰጠውን ተልእኮ በመውሰድ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ጥናቶችን በማጥናት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለዩ የትኩረት መስኮች ላይ ፖሊሲዎች ከመነደፋቸው በፊት የምርምር ስራዎች እንደሚሰሩ አንስተው፤ ተፈጻሚ ከሆኑ በኋላም ምን አይነት ውጤት አመጣ የሚለው እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል።

ለአንድ ሀገር እድገት ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱም እንደ ሀገር የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አመላክተዋል።

በዚህ አመትም በኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 35 ጥናቶች መጠናታቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026