የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አቡዳቢ ዕለታዊ አዲስ የመንገደኞች በረራ ጀመረ

Jul 16, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች አቡዳቢ ከተማ በየቀኑ የሚደረግ አዲስ የመንገደኞች በረራ ጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ ሀማድ ፋሪድና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ80 አመታት ገደማ አፍሪካን ከመላው ዓለም እያስተሳሰረ የቆየ ግዙፍ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።


በዛሬው እለትም ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች አቡዳቢ የተጀመረው አዲስ የበረራ መስመር የሁለቱን ሀገራት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንደሚሆን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ አቡዳቢ የጀመረው የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት በአፍሪካና መካከለኛው ምስራቅ መካከል ያለውን ትስስር የሚያጎለብት ይሆናል ብለዋል።

አየር መንገዱ እ.አ.አ ከ1979 ጀምሮ ወደ ዱባይ የመንገደኞች አገልግሎት በመጀመር ዛሬ ላይ በሳምንት 21 ጊዜ በረራ ያደርጋል ነው ያሉት።

በዛሬው እለትም አየር መንገዱ ከረጅም ጊዜ በኋላ በአዲስ መልክ ወደ አቡዳቢ አገልግሎት መጀመሩ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ተደራሽነት የሚያሰፋ ይሆናል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ሚሲዮን መሪ ሀማድ ፋሪድ፤ የበረራው መጀመር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥ እንደሚያሳድግ ጠቁመዋል።

አየር መንገዱ ከአንድ ወር በፊት ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሻርጃ በሳምንት አራት ጊዜ የሚደረግ አዲስ በረራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026