የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አቡዳቢ ዕለታዊ አዲስ የመንገደኞች በረራ ጀመረ

Jul 16, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች አቡዳቢ ከተማ በየቀኑ የሚደረግ አዲስ የመንገደኞች በረራ ጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ ሀማድ ፋሪድና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ80 አመታት ገደማ አፍሪካን ከመላው ዓለም እያስተሳሰረ የቆየ ግዙፍ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።


በዛሬው እለትም ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች አቡዳቢ የተጀመረው አዲስ የበረራ መስመር የሁለቱን ሀገራት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንደሚሆን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ አቡዳቢ የጀመረው የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት በአፍሪካና መካከለኛው ምስራቅ መካከል ያለውን ትስስር የሚያጎለብት ይሆናል ብለዋል።

አየር መንገዱ እ.አ.አ ከ1979 ጀምሮ ወደ ዱባይ የመንገደኞች አገልግሎት በመጀመር ዛሬ ላይ በሳምንት 21 ጊዜ በረራ ያደርጋል ነው ያሉት።

በዛሬው እለትም አየር መንገዱ ከረጅም ጊዜ በኋላ በአዲስ መልክ ወደ አቡዳቢ አገልግሎት መጀመሩ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ተደራሽነት የሚያሰፋ ይሆናል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ሚሲዮን መሪ ሀማድ ፋሪድ፤ የበረራው መጀመር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥ እንደሚያሳድግ ጠቁመዋል።

አየር መንገዱ ከአንድ ወር በፊት ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሻርጃ በሳምንት አራት ጊዜ የሚደረግ አዲስ በረራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026