
ሰቆጣ ፤ ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ለ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ መዋሉን የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ ይህንኑ ግብአት ተጠቅመው የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው በአስተዳደሩ የሰቆጣ ወረዳ አርሶ አደሮች ገልጸዋል።
የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ ውሏል።

የአርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በዚህም የሰብል ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ የተጠናከረ የባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ጥቅም ላይ ከማዋልም ባለፈ እርጥበትን ማቀብ የሚያስችሉ አነስተኛ ጉድጓዶች በማሳ ላይ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
በሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሳይዳ ቀበሌ አርሶ አደር ይመር አበበ በሰጡት አስተያየት፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ቀጣይነት ያለው ምርታማነትን ለማሳደግ አጋዥ እንደሆናቸው ተናግረዋል።

በየዓመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እያዘጋጁ ተጠቃሚ እንደሆኑና ወጪም እንደቀነሰላቸው አውስተው፤ ለዘንድሮው የመኽር እርሻ በግብአትነት የሚውል ሶስት ሜትር ስፋት በሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በባለሙያ ታግዘው በመቆፈር የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በበጋ ወራት ያዘጋጁትን ማዳበሪያም በግማሽ ሄክታር የእርሻ መሬታቸው ላይ ጥቅም ላይ አውለው ስንዴ መዝራታቸውን አርሶ አደር ይመር ተናግረዋል።
ሌላው አርሶ አደር ገብረየስ በለጠ በበኩላቸው፤ 60 ኩንታል የተፈጥሮ ማዳበሪያ በፍግ አዘጋጅተው በእርሻ ማሳቸው ላይ በመበተን ጥቅም ላይ እንዳዋሉ ገልጸዋል።

የተፈጥሮ አፈር ማዳበሪያ መጠቀም መቻላችን ዘላቂ የሆነ የአፈር ለምነትን ጠብቆ ያቆይልናል ያሉት አርሶ አደር ገብረየስ፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው አስረድተዋል።
በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በምርት ዘመኑ 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በተለያየ የሰብል ዘር ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከግብርና መምሪያው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026