የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በብሔረሰብ አስተዳደሩ ለምርት ዘመኑ 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ ዋለ

Jul 23, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ ፤ ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ለ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ መዋሉን የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ ይህንኑ ግብአት ተጠቅመው የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው በአስተዳደሩ የሰቆጣ ወረዳ አርሶ አደሮች ገልጸዋል።

የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን 230 ሺህ 909 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ ውሏል።


የአርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በዚህም የሰብል ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ የተጠናከረ የባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ጥቅም ላይ ከማዋልም ባለፈ እርጥበትን ማቀብ የሚያስችሉ አነስተኛ ጉድጓዶች በማሳ ላይ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሳይዳ ቀበሌ አርሶ አደር ይመር አበበ በሰጡት አስተያየት፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ቀጣይነት ያለው ምርታማነትን ለማሳደግ አጋዥ እንደሆናቸው ተናግረዋል።


በየዓመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እያዘጋጁ ተጠቃሚ እንደሆኑና ወጪም እንደቀነሰላቸው አውስተው፤ ለዘንድሮው የመኽር እርሻ በግብአትነት የሚውል ሶስት ሜትር ስፋት በሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በባለሙያ ታግዘው በመቆፈር የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

በበጋ ወራት ያዘጋጁትን ማዳበሪያም በግማሽ ሄክታር የእርሻ መሬታቸው ላይ ጥቅም ላይ አውለው ስንዴ መዝራታቸውን አርሶ አደር ይመር ተናግረዋል።

ሌላው አርሶ አደር ገብረየስ በለጠ በበኩላቸው፤ 60 ኩንታል የተፈጥሮ ማዳበሪያ በፍግ አዘጋጅተው በእርሻ ማሳቸው ላይ በመበተን ጥቅም ላይ እንዳዋሉ ገልጸዋል።


የተፈጥሮ አፈር ማዳበሪያ መጠቀም መቻላችን ዘላቂ የሆነ የአፈር ለምነትን ጠብቆ ያቆይልናል ያሉት አርሶ አደር ገብረየስ፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ የእርሻ ስራቸውን በወቅቱ ለማከናወን ይበልጥ እንደጠቀማቸው አስረድተዋል።

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በምርት ዘመኑ 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በተለያየ የሰብል ዘር ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከግብርና መምሪያው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026