የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች ነው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

በአፍሪካ የምግብ ስርዓት ላይ ያተኮረ የአፍሪካ ሼፎች ስብሰባ እና የፖሊሲ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።


''ምግቤ አፍሪካዊ ነው''በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ሼፎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር አማካሪ ሀና አበበ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ስነ-ምህዳሮቿን ለመጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራች ነው።

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በደን መልሶ ልማት እና የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተሰራውን ውጤታማ ስራንም ለአብነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ለማጣጣም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎች መውሰዷን አስታውቀዋል፡፡

ፖሊሲው የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ለምነት መመለስ፣አርሶ አደሮችን በተለይም ሴቶችን እና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም ዘላቂ ፍጆታን ማበረታታት ላይ ማተኮሯን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት ጋር በተለያዩ ደረጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።

ጉባኤው መንግስት እና የሲቪል ማህበረሰቡ አባላት በአህጉሪቱ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በጋራ እንዲሰሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት የቦርድ አባል ፋሲል ገበየው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ፍትሃዊና ዘላቂ የአፍሪካ የምግብ ስርዓት ለመፍጠር በትብብር መስራት እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026