
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።
በአፍሪካ የምግብ ስርዓት ላይ ያተኮረ የአፍሪካ ሼፎች ስብሰባ እና የፖሊሲ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።

''ምግቤ አፍሪካዊ ነው''በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ሼፎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር አማካሪ ሀና አበበ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ስነ-ምህዳሮቿን ለመጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራች ነው።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በደን መልሶ ልማት እና የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተሰራውን ውጤታማ ስራንም ለአብነት ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ለማጣጣም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎች መውሰዷን አስታውቀዋል፡፡
ፖሊሲው የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ለምነት መመለስ፣አርሶ አደሮችን በተለይም ሴቶችን እና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም ዘላቂ ፍጆታን ማበረታታት ላይ ማተኮሯን አብራርተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት ጋር በተለያዩ ደረጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
ጉባኤው መንግስት እና የሲቪል ማህበረሰቡ አባላት በአህጉሪቱ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በጋራ እንዲሰሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።
የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት የቦርድ አባል ፋሲል ገበየው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ፍትሃዊና ዘላቂ የአፍሪካ የምግብ ስርዓት ለመፍጠር በትብብር መስራት እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026