
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።
በአፍሪካ የምግብ ስርዓት ላይ ያተኮረ የአፍሪካ ሼፎች ስብሰባ እና የፖሊሲ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።

''ምግቤ አፍሪካዊ ነው''በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ሼፎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር አማካሪ ሀና አበበ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ስነ-ምህዳሮቿን ለመጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራች ነው።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በደን መልሶ ልማት እና የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተሰራውን ውጤታማ ስራንም ለአብነት ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ለማጣጣም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎች መውሰዷን አስታውቀዋል፡፡
ፖሊሲው የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ለምነት መመለስ፣አርሶ አደሮችን በተለይም ሴቶችን እና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም ዘላቂ ፍጆታን ማበረታታት ላይ ማተኮሯን አብራርተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት ጋር በተለያዩ ደረጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
ጉባኤው መንግስት እና የሲቪል ማህበረሰቡ አባላት በአህጉሪቱ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በጋራ እንዲሰሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።
የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት የቦርድ አባል ፋሲል ገበየው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ፍትሃዊና ዘላቂ የአፍሪካ የምግብ ስርዓት ለመፍጠር በትብብር መስራት እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026