የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች ነው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርናን ለመተግበር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

በአፍሪካ የምግብ ስርዓት ላይ ያተኮረ የአፍሪካ ሼፎች ስብሰባ እና የፖሊሲ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።


''ምግቤ አፍሪካዊ ነው''በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ሼፎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሀላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር አማካሪ ሀና አበበ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ስነ-ምህዳሮቿን ለመጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራች ነው።

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በደን መልሶ ልማት እና የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተሰራውን ውጤታማ ስራንም ለአብነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ለማጣጣም የሚያስችሉ የፖሊሲ እርምጃዎች መውሰዷን አስታውቀዋል፡፡

ፖሊሲው የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ የተራቆቱ መሬቶችን ወደ ለምነት መመለስ፣አርሶ አደሮችን በተለይም ሴቶችን እና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም ዘላቂ ፍጆታን ማበረታታት ላይ ማተኮሯን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት ጋር በተለያዩ ደረጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።

ጉባኤው መንግስት እና የሲቪል ማህበረሰቡ አባላት በአህጉሪቱ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በጋራ እንዲሰሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት የቦርድ አባል ፋሲል ገበየው (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ፍትሃዊና ዘላቂ የአፍሪካ የምግብ ስርዓት ለመፍጠር በትብብር መስራት እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026