የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በቀጣናው የምግብ ስርዓት ሽግግርን ለማሳለጥ በአህጉራዊ የትብብር ማዕቀፍ እንሰራለን - የኢጋድ አባል ሀገራት

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በቀጣናው የምግብ ስርዓትን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በአህጉራዊ ማዕቀፍ በጋራ እንደሚሰሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን /ኢጋድ/ አባል ሀገራት አስታወቁ፡፡

የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ያሉ ቀጣናዊ ዕድሎችን በተመለከተ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስብሰባ በትናትናው ዕለት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

ስብሰባው በግብርናው ዘርፍ አንገብጋቢ የሆኑ ችግሮችን በመለየት ለመፍታትና ለ2ኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለማዘጋጀት ያለመ ነው፡፡


ይሄንን ተከትሎ የኢጋድ ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ን ጨምሮ የአባል ሀገራቱ ሚኒስትሮች በተገኙበት የተደረገው ስብሰባ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡

በኢጋድ ቀጣና የስርዓተ ምግብ ሽግግር በማሳለጥ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ረሃብን መከላከል የሚያስችል አህጉራዊ የቅንጅት ማዕቀፍ እንደሚፈጥሩ አረጋግጠዋል፡፡

ቴክኖሎጂዎችና የተሻሻሉ የምርጥ ዘር ዝርያዎችን በመጠቀም እንዲሁም የስርዓተ ምህዳር ብዝሃነትን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

ዘላቂ የመሬትና ውሃ አጠቃቀምን በማስፋት ስነ ምህዳርን የመቋቋም አቅም ያላቸው ዝርያዎችን ማስፋት በትኩረት ይሰራበታልም ተብሏል፡፡

የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል ቀጣናዊ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን ማጠናከር፣ የአደጋ ጊዜ እቅድ ማውጣትና እንደ በረሀ አንበጣ ያሉ ተባዮች እና የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በትብብር እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡

የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከልና የልማት የፋይናንስ አማራጮችን ያካተተ አዳዲስ የፋይናንስ ሥልት እንዲዳብር ይደረጋል ተብሏል፡፡

ተቋማዊ አቅምን፣ የፋይናንስ ስርዓቱን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማትን ከቀጣናዊ ፖሊሲዎች ጋር በማጣጣም ምቹ አሰራር እንደሚፈጠር ተገልጿል፡፡

በኢጋድ አስተባባሪነት የተቀናጀ ቀጣናዊ የቴክኒክ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም እንደሚደግፉም ተጠቁሟል፡፡

የአባል ሀገራቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በኢጋድ ዋና ጸሀፊ አስተባባሪነት የጋራ ፕሮግራሞች ተቀርጸው ውይይቶች ይዘጋጃሉ ተብሏል፡፡

በኢጋድ እና በአጋሮቹ አመቻችነት የቀጣይ የቴክኒክ ኮሚቴው ስብሰባ በስድስት ወራት ውስጥ እንዲጠራ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026