የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ነው

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ ከደረሰኝ አቆራረጥ ጋር ተያይዞ የተጠናከረ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ 82 ነጋዴዎች ላይ 7 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ቅጣት እንደተጣለባቸውና ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸውም ጽህፈት ቤቱ አስታውቀዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በዞኑ ከመዘጋጃ ቤታዊ፣ ከቀጥታ ታክስ እና ቀጥታ ካልሆነ ታክስ 4 ነጥብ 17 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉም ተመላክቷል።

የምስራቅ ሸዋ ዞን ገቢዎች ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ በድሪያ ረሽድ ለኢዜአ እንደገለጹት ጽህፈት ቤቱ ለዞኑ ህዝብ ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ገቢ ለመሰብሰብ ሲሰራ ቆይቷል።

በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዞኑን ገቢ ለማሳደግ በተደረገው ጥረት የሚሰበሰበው ገቢ መሻሻል ማሳየቱን አመላክተዋል።

በዚህ ረገድ የዞኑ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ሀብት አኳያ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ነው የሚናገሩት።

በ2017 በጀት ዓመት ከማዘጋጃ ቤታዊ፣ ከታክስ ኦዲት፣ ከቀጥታ ታክስ እና ቀጥታ ካልሆነ ታክስ 4 ነጥብ 17 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከእቅድ በላይ 4 ነጥብ 25 ቢሊዮን ብር ገቢ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

መቂና መተሐራ ከተሞችን ጨምሮ ከ11 ወረዳዎች የተሰበሰበው የገቢ አፈጸፃጸም ካለፉት ዓመታት ከነበረው ገቢ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ለውጥና መሻሻል የታየበት መሆኑንም አመላክተዋል።

ለገቢው ማደግ አስተዋጽኦ ካደረጉት መካከል የገቢ አሰባሰብ አሠራሩን በማዘመን ግብር ከፋዮች ከሰው ንክኪና ብልሹ አሠራር በፀዳ መልኩ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ዘመናዊ የኢ-ታክስ አገልግሎት ተግባራዊ መደረጉ ተጠቃሽ መሆኑን አስረደተዋል።

እንዲሁም የግብር ሥርዓት ውስጥ ያልገቡትን በሕጉ መሠረት ወደ ግብር ሥርዓቱ እንዲገቡ በማድረግና ወቅቱን ያላገናዘብ ግብር የሚከፍሉትም ወቅታዊ እንዲሆኑ መደረጉ ለገቢው ማደግና ውጤት መገኘት አስተዋጽኦ ማድረጉን አውስተዋል።

በተለይም የንግዱ ማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማጎልበት፤ የሕግ ማስከበር ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ መሠራቱ፣ በየደረጃው የአገልጋይነት ስሜት እንዲጎለብት አሠራርን በማሻሻልና በማዘመን በገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳደር መቻሉን አብራርተዋል፡፡

ለግብር ከፋዮች የተፈጠረው ምቹና የተሳለጠ የክፍያ ሥርዓት የገቢ አቅምን አሳድጓል ያሉት ኃላፊዋ በአሁኑ ወቅት በዞኑ ደረጃ “ሀ” ፣ “ለ” እና “ሐ” 12 ሺህ 617 ግብር ከፋዮች እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

በቀጣይም የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻልና በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ የታክስ ማሳወቅና የታክስ ኦዲት ስራዎችን ማጠናከር የገቢ አቅምን ለማጎልበት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ ከደረሰኝ አቆራረጥ ጋር ተያይዞ የተጠናከረ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ 82 ነጋዴዎች ላይ 7 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ቅጣት እንደተጣለባቸውና ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026