
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን በመጠቀም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ።
ከሁለተኛ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ጎን ለጎን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።
ሚኒስትሮቹ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በውይይታቸው አንስተዋል።
የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያላትን አቅምና እያከናወነች ያለውን ተግባር አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ቡናና የእንስሳት ውጤቶችን ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እንደምትልክ ገልጸው፤ ይህንን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
ኢትዮጵያ በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ አማራጮች እንዳላት በመጥቀስ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ማቀነባበሪያ፣ማዳበሪያ ፋብሪካና ሌሎች ዘርፎች መሰማራት የሚችሉባቸው አማራጮች እንደሆኑ አብራርተውላቸዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸውዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሚኒስትሮች በሁለቱ አገራት መካከል በግብርና፤ንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ለመጠቀም ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ለመስራት ተስማምተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026