የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ከኢትዮጵያ የስንዴ ምርትና የሌማት ትሩፋት ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገለጹ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ኢኒሼቲቭና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ካስመዘገበችው ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በተጓዳኝ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል።


ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ እና ከሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢ እና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ ጋር ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ ማሻሻያዎችን በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማግኘቷን አብራርተዋል፡፡

እንዲሁም በንግድና ሌሎች ዘርፎች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ተግባር አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ እያቀረበች መሆኗን በመግለጽ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም አህጉራዊ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።

ከሁለቱ ሀገራት ጋር በተለያዩ የግብርና ዘርፎች በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ትብብሮችን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ በበኩላቸው ሀገራቸው በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በስንዴ፣ በሌማት ትሩፋት እና በሌሎች የግብርና ዘርፎች ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል።

ዛምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት በመፈራረም በዘርፉ በጋራ መስራት እንደምትፈልግ ሚኒስትሩ አንስተዋል።

የሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጠንካራ የግብርና ሥርዓት በመገንባት ካስመዘገበችው ስኬት ትምህርት መውሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

በተለይም የስንዴ ምርትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተመዘገቡ ስኬቶች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ነው ያነሱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026