
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ኢኒሼቲቭና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ካስመዘገበችው ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በተጓዳኝ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል።

ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ እና ከሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢ እና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ ጋር ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ ማሻሻያዎችን በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማግኘቷን አብራርተዋል፡፡
እንዲሁም በንግድና ሌሎች ዘርፎች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ተግባር አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ እያቀረበች መሆኗን በመግለጽ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም አህጉራዊ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።
ከሁለቱ ሀገራት ጋር በተለያዩ የግብርና ዘርፎች በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ትብብሮችን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ በበኩላቸው ሀገራቸው በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በስንዴ፣ በሌማት ትሩፋት እና በሌሎች የግብርና ዘርፎች ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል።
ዛምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት በመፈራረም በዘርፉ በጋራ መስራት እንደምትፈልግ ሚኒስትሩ አንስተዋል።
የሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጠንካራ የግብርና ሥርዓት በመገንባት ካስመዘገበችው ስኬት ትምህርት መውሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
በተለይም የስንዴ ምርትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተመዘገቡ ስኬቶች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ነው ያነሱት።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026