
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ኢኒሼቲቭና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ካስመዘገበችው ስኬት ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በተጓዳኝ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል።

ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ እና ከሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢ እና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ ጋር ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ ማሻሻያዎችን በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማግኘቷን አብራርተዋል፡፡
እንዲሁም በንግድና ሌሎች ዘርፎች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ተግባር አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ እያቀረበች መሆኗን በመግለጽ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም አህጉራዊ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።
ከሁለቱ ሀገራት ጋር በተለያዩ የግብርና ዘርፎች በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ትብብሮችን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሩበን ምቶሎ በበኩላቸው ሀገራቸው በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በስንዴ፣ በሌማት ትሩፋት እና በሌሎች የግብርና ዘርፎች ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች ልምድ መቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል።
ዛምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት በመፈራረም በዘርፉ በጋራ መስራት እንደምትፈልግ ሚኒስትሩ አንስተዋል።
የሞዛምቢክ የግብርና፣ አካባቢና አሳ ሃብት ሚኒስትር ሮቤርቶ ሚቶ አልቢኖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጠንካራ የግብርና ሥርዓት በመገንባት ካስመዘገበችው ስኬት ትምህርት መውሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
በተለይም የስንዴ ምርትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተመዘገቡ ስኬቶች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ነው ያነሱት።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026