የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሳይበር ደህንነት ወር የህብረተሰቡን ንቃተ-ህሊና ማጎልበት የሚያስችሉ የንቅናቄ ተግባራት ይከናወናሉ

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፡-በስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የህብረተሰቡን ንቃተ-ህሊና ማጎልበት የሚያስችሉ የንቅናቄ ተግባራት እንደሚከናወኑ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሃሚድ ገለጹ፡፡

ስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት-የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 1 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይከበራል፡፡

ወሩን በማስመልከት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሃሚድ በሰጡት መግለጫ፥ የሳይበር ጥቃት በዓለም አቀፍ ደረጃ በቁጥርም ሆነ በአይነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል ብለዋል።

የሳይበር ደህንነት ወር መከበር ዋነኛ ዓላማው የዜጎችንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ የሚያጎለብቱ የንቅናቄ መድረኮችን በማዘጋጀት ሀገራዊ የሳይበር ደህንነት የመከላከል አቅምን ማሳደግ ነው።

የተቋማት አሰራር በስፋት ዲጂታላይዝ እየተደረገ በመሆኑ ከወዲሁ የሳይበር ደህንነት ዝግጁነታቸው እንዲጨምር የሚያስችሉ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል፡፡

የማህበረሰቡና የተቋማት የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና አነስተኛ በመሆኑ መጠነ-ሰፊ ሃገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና ማጎልበቻ ንቅናቄ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል፡፡

“የሳይበር ደህንነት-የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የመጀመሪያው የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅት፣ ቁጥጥርና ስርጭትን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁለተኛ ደረጃ በዲጂታላይዜሽን ደህንነት ጉዞ የተቋማትን የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የሳይበር ደህንነት ወር የመክፈቻ መርሃ ግብር ጥቅምት 1 ቀን 2018 እንደሚካሄድ ጠቅሰው ወሩን ሙሉ በተለያዩ ከተሞች የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና የሚያሳድጉ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026