የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬት ሚናው የላቀ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬት ሚናው የላቀ መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ከተጀመረ ወዲህ እስካሁን 25 ሚሊዮን ዜጎች ምዝገባ ማከናወናቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እና አስፈላጊነት ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄዷል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ ዘርፍ ኃላፊ ሔኖክ ጥላሁን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች ዘርፈ ብዙ አገልግሎትን በተቀላጠፈ እና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።

ፕሮግራሙ ከተጀመረ እስከ አሁን ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ 25 ሚሊዮን ዜጎች ምዝገባ ማከናወናቸውን ጠቅሰው፥ በ2018 በጀት ዓመት 40 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል።

ፋይዳ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችልና በህጋዊ መንገድ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ስደተኞችንም እንደሚያካትት ኃላፊው ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነት ቁልፍ ሚናን የሚጫወት ነው ብለዋል።

ህብረተሰቡ የፋይዳን አስፈላጊነት ተገንዝቦ እንዲመዘገብ የአመራሩ የጋራ ጥረት እንደሚጠበቅም አንስተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው፥ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ሁሉንም የሚያካትት መርሃግብር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፋይዳ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያረጋግጥ የሀገርን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ በመሆኑ መንግስት በትኩረት እየሰራበት ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ሁሉም ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከ355 ሺህ በላይ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መታቀዱም ተገልጿል።

በመድረኩ ላይ የክልል፣የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም አጋር አካላቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025