የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በባሕርዳር  እየተከናወኑ  የሚገኙ  አበረታች  የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት እንደሀገር የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ መሆናቸው ተመላከተ።

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራ ቡድን በባሕርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።


በዚህ ወቅት ከንቲባው አለማየሁ አሰፋ ፤ ኮሪደርን ጨምሮ ደረጃቸውን የጠበቁ የመንገድ መሰረተ ልማቶችና ወደ ጣና የሚያስገቡ መንገዶች፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫና ሌሎችንም የግንባታ ተግባራት ተዘዋውረው መመልከታቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራት ባሕር ዳርን ይበልጥ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማቱን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ጣናን ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች የመግለጥ ተግባር ከተማዋን ሳቢና ማራኪ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።

እየተገነቡ የሚገኙት የልማት ተግባራት የሕዝብ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ እንደሆኑ መገንዘባቸውን ጠቁመው፤ ይህም ሀገሪቱ ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር የጀመረችውን ጉዞ ለማፋጠን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።


አመራሩ ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እየተጋ መሆኑን ማረጋገጣቸውን ያነሱት ከንቲባው፤ ከባሕርዳር ያገኙትን ልምድና ተሞክሮ በቢሾፍቱ በሚገኙ የኃይቅ ዳርቻዎች ተግባራዊ በማድረግ የከተማቸውን ዕድገት ለማፋጠን እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ከተማን ዕድገት የሚያፋጥኑ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


የከተማዋን ሰላም በማፅናት የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ፣ ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ የአረንጓዴና ሌሎች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራው ቡድን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን መመልከቱ የጋራ የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች ወደ ቢሾፍቱ ከተማ አቅንተው በመጎብኘት ግንኙነቱንና ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሰሩም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026