የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በባሕርዳር  እየተከናወኑ  የሚገኙ  አበረታች  የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት እንደሀገር የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ መሆናቸው ተመላከተ።

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራ ቡድን በባሕርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።


በዚህ ወቅት ከንቲባው አለማየሁ አሰፋ ፤ ኮሪደርን ጨምሮ ደረጃቸውን የጠበቁ የመንገድ መሰረተ ልማቶችና ወደ ጣና የሚያስገቡ መንገዶች፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫና ሌሎችንም የግንባታ ተግባራት ተዘዋውረው መመልከታቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራት ባሕር ዳርን ይበልጥ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማቱን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ጣናን ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች የመግለጥ ተግባር ከተማዋን ሳቢና ማራኪ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።

እየተገነቡ የሚገኙት የልማት ተግባራት የሕዝብ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ እንደሆኑ መገንዘባቸውን ጠቁመው፤ ይህም ሀገሪቱ ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር የጀመረችውን ጉዞ ለማፋጠን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።


አመራሩ ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እየተጋ መሆኑን ማረጋገጣቸውን ያነሱት ከንቲባው፤ ከባሕርዳር ያገኙትን ልምድና ተሞክሮ በቢሾፍቱ በሚገኙ የኃይቅ ዳርቻዎች ተግባራዊ በማድረግ የከተማቸውን ዕድገት ለማፋጠን እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ከተማን ዕድገት የሚያፋጥኑ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


የከተማዋን ሰላም በማፅናት የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ፣ ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ የአረንጓዴና ሌሎች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራው ቡድን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን መመልከቱ የጋራ የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች ወደ ቢሾፍቱ ከተማ አቅንተው በመጎብኘት ግንኙነቱንና ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሰሩም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025