የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መንግሥት ለግብርና ኢንቨስትመንት መስፋፋት በፖሊሲ የተደገፈ ትኩረት ሰጥቷል- ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የግብርና ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋፅኦ እንዲጨምር በፖሊሲ የተደገፈ ትኩረት መስጠቱን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ፡፡

ግብርና በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፣ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ከመያዙም በላይ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለምግብ ዋስትና እና ለውጭ ምንዛሪ ገቢ ዋና ምንጭ ነው።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ በመገኘት፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው በሰብል፣ በአትክልት፣ በፍራፍሬ እና በቅመማ ቅመም ልማት የተሰማሩ የግል ባለሀብቶችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።


ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ በግብርና ኢንቨስትመንት የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ተሳትፎ ለማበረታታት መንግሥት የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የድጋፍ ፓኬጆችን በማዘጋጀት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰብል ልማት ዘርፍ ብቻ ከ6 ሺህ በላይ ባለሀብቶች ወደ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ወስደው እየሠሩ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህም ውስጥ 720 ሺህ ሄክታሩ ወደ ልማት ገብቷል ብለዋል።

ይህም በተለይ በቆላማ አካባቢዎች ታርሰው የማይታወቁ መሬቶች እንዲለሙ አስችሏል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ የግብርና እምቅ አቅሟን ተጠቅማ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት የባለሀብቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

መንግሥት በሚቀጥሉት ጊዜያት ለግብርና ኢንቨስትመንት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመው፣ አዲስ በወጣው የግብርናና የገጠር ልማት ፖሊሲ ከዋነኛ ምሰሶዎች መካከል አንዱ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ልማት ግቦች የሆኑትን ምግብ ዋስትና ማረጋገጥ፣ አካታች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓት ማምረት፣ የኤክስፖርት ገቢን ማሳደግና ገቢ ምርቶችን መተካትን ለማሳካት የግል ባለሀብቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

የባለሀብቶችን ተሳትፎ ለማጠናከርና የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በመለየት አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለስኬታማነታቸው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በግብርና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው የሚገኙት አቶ ዳኜ ዳባ በበኩላቸው፤ በሰብል፣ በቅመማ ቅመም፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ውጤታማ ሥራ እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ቀደም ሲል ከልማት ውጭ የነበረን መሬት ወደ ልማት በማስገባት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።

የግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ፣ የምግብና ሥርዓተ ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሎም ለሀገራዊ ምጣኔ ዕድገት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025