የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መንግሥት ለግብርና ኢንቨስትመንት መስፋፋት በፖሊሲ የተደገፈ ትኩረት ሰጥቷል- ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የግብርና ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋፅኦ እንዲጨምር በፖሊሲ የተደገፈ ትኩረት መስጠቱን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ፡፡

ግብርና በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፣ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ከመያዙም በላይ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለምግብ ዋስትና እና ለውጭ ምንዛሪ ገቢ ዋና ምንጭ ነው።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ በመገኘት፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው በሰብል፣ በአትክልት፣ በፍራፍሬ እና በቅመማ ቅመም ልማት የተሰማሩ የግል ባለሀብቶችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።


ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ በግብርና ኢንቨስትመንት የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ተሳትፎ ለማበረታታት መንግሥት የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የድጋፍ ፓኬጆችን በማዘጋጀት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰብል ልማት ዘርፍ ብቻ ከ6 ሺህ በላይ ባለሀብቶች ወደ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ወስደው እየሠሩ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህም ውስጥ 720 ሺህ ሄክታሩ ወደ ልማት ገብቷል ብለዋል።

ይህም በተለይ በቆላማ አካባቢዎች ታርሰው የማይታወቁ መሬቶች እንዲለሙ አስችሏል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ የግብርና እምቅ አቅሟን ተጠቅማ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት የባለሀብቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

መንግሥት በሚቀጥሉት ጊዜያት ለግብርና ኢንቨስትመንት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመው፣ አዲስ በወጣው የግብርናና የገጠር ልማት ፖሊሲ ከዋነኛ ምሰሶዎች መካከል አንዱ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ልማት ግቦች የሆኑትን ምግብ ዋስትና ማረጋገጥ፣ አካታች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓት ማምረት፣ የኤክስፖርት ገቢን ማሳደግና ገቢ ምርቶችን መተካትን ለማሳካት የግል ባለሀብቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

የባለሀብቶችን ተሳትፎ ለማጠናከርና የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በመለየት አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለስኬታማነታቸው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በግብርና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው የሚገኙት አቶ ዳኜ ዳባ በበኩላቸው፤ በሰብል፣ በቅመማ ቅመም፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ውጤታማ ሥራ እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ቀደም ሲል ከልማት ውጭ የነበረን መሬት ወደ ልማት በማስገባት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።

የግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የግብርና ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ፣ የምግብና ሥርዓተ ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሎም ለሀገራዊ ምጣኔ ዕድገት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026