የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የባህር በር ጥያቄው ከፍትሃዊ ተጠቃሚነት እሳቤ የመነጨና የህልውና ጉዳይ ነው- ምሁራን

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ጥያቄው ኢትዮጵያ ከምትከተለው የፍትሃዊ ተጠቃሚነት እሳቤ የመነጨና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ሊደገፍ ይገባል ሲሉ የመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ።

የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ኃብት አጠቃቀምና የሃይድሮሎጂ ረዳት ፕሮፌሰር አለማየሁ አባተ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሰሚነቷን በተሻለ መልኩ የሚያሳድግ ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ ነው።


ኢትዮጵያ የግዙፍ ኢኮኖሚና ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ባለቤት እንዲሁም ለቀይ ባህር በቅርብ ርቀት የምትገኝ መሆኗ ከሌሎች ወደብ አልባ አገራት ልዩ እንደሚያደርጋት የዓለም አቀፍ ተሞክሮን በማጣቀስ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብትን በፍትሃዊነት መጠቀም በሚለው እሳቤ የምታምንና እሳቤውንም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ በተግባር ማሳየቷን ጠቅሰዋል።

ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ከፍትሃዊ ተጠቃሚነት እሳቤ የሚመነጭና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ሊደገፍ ይገባል ሲሉ አስረድተዋል።

የባህር በር ጥያቄው ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ መገንባት እንድትችል እና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፍትሃዊ የባህር በር ጥያቄ የብሔራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ፍላጎቱን እውን ለማድረግ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ያሉት በዩኒቨርሲቲው የውኃና መስኖ የትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ አቶ ተስፋሁን አዲሱ ናቸው።


ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ፍትሀዊ ባልሆነ መንገድ ወደብ አልባ መሆኗ የሚያስቆጭ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ የባሕር በር ስለሌላት ብቻ በዓለም አቀፍ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የገቢና ወጪ የንግድ ሥርዓት ውስጥ ለከፍተኛ ወጪ ስትዳረግ መቆየቷን አስታውስዋል።

አሁን የጀመረችው ጥረት ከቀጣናው አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሰሚነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን የሚያሳድግ በመሆኑ ጥያቄው በሁሉም ዘንድ ሊታገዝ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026