የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የዋጋ ንረትን የሚያረጋጉ አሠራሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ)፡- 219 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ጨምሮ በአምሥት የገበያ ማዕከላት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት በበቂ ሁኔታ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።

የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አሸናፊ ብርሃኑ እንዳሉት፤ 219 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ጨምሮ በአምሥት የገበያ ማዕከላት የዋጋ ንረትን ያረጋጋ ግብይት እየተከናወነ ነው።

ለእነዚህ ገበያዎችና ማዕከላት የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርት በበቂ ሁኔታ ከሥር ሥር እየቀረበ መሆኑንም ለኢዜአ አረጋግጠዋል።

በየሳምንቱ እየወጣ ባለው የዋጋ ተመን መሠረት ግብይት እንደሚከናወንም አስረድተዋል።

ከሌሎች ነጻ ገበያዎች አንጻር በቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በአምሥቱ ገበያ ማዕከላት በአማካይ ከ20 በመቶ በላይ ቅናሽ ተደርጎ እንደሚሸጥም ተናግረዋል።

በሁሉም የመዲናዋ ወረዳዎች የቅዳሜና እሁድ ገበያ መኖሩን ጠቅሰው፤ ከፍላጎት ማደግ አንጻር በቀጣይ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን የማስፋት ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን አመላክተዋል።

በዚህም መሰረት አንድ የቅዳሜና እሁድ ገበያ ስፍራ ባላቸው ወረዳዎች ተጨማሪ እንዲኖር ይደረጋል ብለዋል።

እነዚህ የገበያ አማራጮች በተቀመጠው አሠራር መፈጸማቸውን የሚከታተሉ ሱፐር ቫይዘሮች መመደባቸውን እና 1 ሺህ 216 የግብይት ተቆጣጣሪዎች በስምሪት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ሕገ ወጥ ድርጊት ሲፈጽሙ የተገኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያ ሻጮች ከትስስር ውጭ እንደሚደረጉ እና በሕግም ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026