🔇Unmute
አምቦ ፤ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፡- አምቦ ዩኒቨርሲቲ የአርሶ አደሩን የግብርና ምርታማነት ማሳደግ የሚያስችሉ ዝርያዎችን በምርምር በማወጣት እየደገፈ መሆኑን ገለጸ።
በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የተመራ ቡድን በጉደር ማሞ መዘመር ካምፓስ በምርምር የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የግብርና ሥራዎችን በመስክ ተመልክቷል።

በወቅቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ(ዶ/ር) እንዳመለከቱት፤ ተቋሙ ከመማር ማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን የአካባቢውን ማህበረሰብ ህይወት ለማሻሻል የሚያስችሉ ምርምሮችን እያካሄደ ነው።
ሌሎች ድርጅቶችን በማሳተፍ ጭምር የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ የሚያስችሉ የሰብል ዝሪያዎችን በምርምር አውጥቶ ለአርሶ አደሮች ማከፋፈሉን አንስተዋል።
የአካባቢው አርሶ አደር የቀረቡለትን የተሻሻሉ የሰብል ዝሪያዎች የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም ምርታቸውን ማሳደግ እንዲቻል በተከታታይ የባለሙያዎች ድጋፍ ተደርጎለታል ብለዋል።

በዚህም አርሶ አደሩ ውጤታማ መሆኑን ያመለከቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት፤ በተጨማሪም የወተት ላሞች እርባታ ፤ የዶሮ እርባታ እና የማር ምርት ከዩኒቨርሲቲው ማሕብረሰብ ባሻገር ለአካባቢው ነዋሪዎች በማቅረብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
የዛሬው የመስክ ጉብኝት ዓላማም ዩኒቨርሲቲው የምርምርና የማሕበረሰብ አገልግሎቶችን ለባለድርሻ አካላት ማሳወቅ ብሎም ከሌሎች የምርምር ተቋማት ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የጉደር ማሞ መዘመር ካምፖስ ዳይሬክተር ንጉሴ በቀለ ( ዶ/ር ) ናቸው፡፡

በካምፓሱ የሰብል ምርምር ፤ የወተት ላሞች እና የዶሮ እርባታዎችን አርሶ አደሩና ሌላውም ማህበረሰብ በማሳተፍ ጭምር በመደገፍ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ሌላው የመስክ ጉብኝቱ ላይ የተገኙት የግብርና ተማራማሪ ተስፋዬ ሽፈራው(ዶ/ር) እንዳሉት፤ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት በሚያደርጉት የምርምር ስራ የተሻለ ውጤት እየተገኘ ነው።
በዚህም ለአካባቢው ነዋሪዎችም በምርምር የተገኙ የተለያዩ የሰብል ዝሪያዎችን፣ የተሻሻሉ የወተት ላሞችንና ዶሮዎችን እያቀረብን ነው ብለዋል።

የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሙሉ እመቤት ኢዶሳ በሰጡት አስተያየት፤ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የጉደር ማሞ መዘመር ካምፓስ የተለያየ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከካምፓሱ ከሶስት ዓመት በፊት የወተት ላም እንደተሰጣቸው ያስታወሱት ወይዘሮ ሙሉእመቤት ፤ ላሟ ሶስት ጥጃዎች በመውለዷ ተጠቃሚ እየሆንኩ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም የተሻሻሉ የሰብል ዝሪያዎችን እንደሰጧቸው ጠቅሰው፤ ተቋሙ ለሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች ተመሳሳይ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025