🔇Unmute
ደሴ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በደሴ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለየዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል።
በመጀመሪያው ዙር ከ1 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት በማከናወን ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ተመልክቷል።

የከተማው አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ እንደገለጹት፣ የበጀት ዓመቱ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ተገብቷል።
በዚህም የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄ እና የከተማውን የእድገትና አሻጋሪ እቅድ መነሻ በማድረግ በተያዘው በጀት ዓመት ከ20 በላይ ፕሮጀክቶች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።
በዚህም ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የበጀት ዓመቱ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ዛሬ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።
ከኮሪደር ልማቱ በተጨማሪ የአንድ ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ የሥራ እድል መፍጠሪያ ሼዶች፣ የጤናና የትምህርት ቤቶች ማስፋፊያ ከፕሮጀክቶቹ መካካል እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።
ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲሰሩ ሕብረተሰቡ ሰላሙን በማፅናት የጀመረውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አንዷለም እሸቱ በበኩላቸው፤ ፕሮጀከቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለዚህም አስፈላጊው ግብዓትና ፕሮጀክቶችን መስራት የሚያስችል ዝግጅት ተደርጎ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ዛሬ መጀመሩን አረጋግጠዋል።

በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፤ ከተማ አስተዳደሩ ሕብረተሰቡን በማስተባበር ጭምር ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ልማት እየሰራ መሆኑን በማንሳት መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ዛሬ የተጀመሩ ልማቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ የድርሻቸውን እንደሚወጡም አስታውቀዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026