የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በተለያየ ምክንያት ምርታማነቱን ያጣ የእርሻ መሬትን በማከም ወደ ልማት እየተመለሰ ነው

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 15/2018(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል በተለያየ ምክንያት ምርታማነቱን ያጣ የእርሻ መሬትን በማከም ወደ ልማት የመመለሱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ባንጉ በቀለ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል።


በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጥሮ ሀብታቸው ተመናምኖ ምርታማነቱን ያጣ አሲዳማ መሬትን በኖራ በማከምና በተፋሰስ በማልማት ወደ እርሻ መሬት እንዲለወጡ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

ተዳፋት የበዛበትን አካባቢና ተራራማ መሬትን ህዝቡን በማስተባበር የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በመሰራቱ ወደ እርሻ ማሳነት መለወጣቸውን ተናግረዋል።


በበንሳ፣ ሀገረ ሰላም፣ ጠጢቻና ሌሎች ደጋማ አካባቢዎች የመሬቱን አሲዳማነት ለማከም ከ80 ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለአርሶ አደሩ በማቅረብ መሬቱን ማከም እንደተቻለም ገልጸዋል።

በክልሉ ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ሀገረ ሰላም ወረዳ ልዩ ኡዱሜ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ፋንታዬ ፉጡኔ እንዳሉት የእርሻ ማሳቸው ተዳፋታማ በመሆኑ በናዳና በመሬት መንሸራተት ሳቢያ ምርታማነቱን አጥቶ ነበር።


ማሳውን በተፋሰስ ልማት ጠረጴዛማ እርከን ስራ መልሶ እንዲያገግም በማድረግና የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት እንዲሁም የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም መልሰው ለእርሻ ስራ እንዲውል ማድረጋቸውን አስረድተዋል።

መሬታቸው በመራቆቱና አሲዳማ በመሆኑ ምክንያት ምርቱ እየቀነሰ በመምጣቱ የሚያመርቱት ምርት ለቤተሰብ እንኳን ሊበቃ እንዳልቻለ ያስታወሱት ደግሞ የወረዳው አለቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር አየለ ጋልፈቶ ናቸው።


አሁን ግን ከአፈር ማዳበሪያው በተጨማሪ ኖራ በመጠቀም ያለሙት ማሳ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝና ከበፊቱ የተሻለ ምርት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 160 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር የተሸፈነ ሲሆን ከዚህም 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026