የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በተለያየ ምክንያት ምርታማነቱን ያጣ የእርሻ መሬትን በማከም ወደ ልማት እየተመለሰ ነው

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 15/2018(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል በተለያየ ምክንያት ምርታማነቱን ያጣ የእርሻ መሬትን በማከም ወደ ልማት የመመለሱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ባንጉ በቀለ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል።


በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጥሮ ሀብታቸው ተመናምኖ ምርታማነቱን ያጣ አሲዳማ መሬትን በኖራ በማከምና በተፋሰስ በማልማት ወደ እርሻ መሬት እንዲለወጡ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

ተዳፋት የበዛበትን አካባቢና ተራራማ መሬትን ህዝቡን በማስተባበር የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በመሰራቱ ወደ እርሻ ማሳነት መለወጣቸውን ተናግረዋል።


በበንሳ፣ ሀገረ ሰላም፣ ጠጢቻና ሌሎች ደጋማ አካባቢዎች የመሬቱን አሲዳማነት ለማከም ከ80 ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለአርሶ አደሩ በማቅረብ መሬቱን ማከም እንደተቻለም ገልጸዋል።

በክልሉ ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ሀገረ ሰላም ወረዳ ልዩ ኡዱሜ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ፋንታዬ ፉጡኔ እንዳሉት የእርሻ ማሳቸው ተዳፋታማ በመሆኑ በናዳና በመሬት መንሸራተት ሳቢያ ምርታማነቱን አጥቶ ነበር።


ማሳውን በተፋሰስ ልማት ጠረጴዛማ እርከን ስራ መልሶ እንዲያገግም በማድረግና የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት እንዲሁም የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም መልሰው ለእርሻ ስራ እንዲውል ማድረጋቸውን አስረድተዋል።

መሬታቸው በመራቆቱና አሲዳማ በመሆኑ ምክንያት ምርቱ እየቀነሰ በመምጣቱ የሚያመርቱት ምርት ለቤተሰብ እንኳን ሊበቃ እንዳልቻለ ያስታወሱት ደግሞ የወረዳው አለቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር አየለ ጋልፈቶ ናቸው።


አሁን ግን ከአፈር ማዳበሪያው በተጨማሪ ኖራ በመጠቀም ያለሙት ማሳ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝና ከበፊቱ የተሻለ ምርት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 160 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር የተሸፈነ ሲሆን ከዚህም 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026