የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የአካባቢውን አርሶ አደሮች ይበልጥ ውጤታማ እያደረገ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወራቤ ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማቅረብ እና በሙያ ያደረገላቸው ድጋፍ የግብርና ልማታቸውን ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን እያገዛቸው መሆኑን በስልጤ ዞን የአሊቾ ውሪሮ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የተከናወኑ ሥራዎች በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ በመስክ ተጎብኝቷል፡፡


በዚህ ወቅት በወረዳው የሽልማት ቀበሌ አርሶ አደር ነስራ ከማል በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራቸውን በባህላዊ መንገድ ስለሚያከናውኑ በልፋታቸው ልክ ውጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በምርምር ማዕከሉ የሚቀርበውን የሰብል ምርጥ ዘርና ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በባለሙያዎች ታግዘው በመተግበር ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እየተሻሻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ማዕከሉ በሰብል ዝርያና በሙያ በሚያደርግላቸው ድጋፍ ውጤታማነታቸው እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ሌላው አርሶ አደር ናሲያ ጃቢር ናቸው፡፡


በተለይ በመስመር መዝራትን ጨምሮ ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተጠቅመው ከሚያለሙት ገብስ፣ ስንዴና አተር የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ዝርያዎቹ ፈጥነው ከመድረስ ባለፈ በምርት ይዘታቸው ከፍተኛና በሽታ መቋቋም የሚችሉ ናቸው ያሉት አርሶ አደሩ፤ በመሥመር መዝራቱም በተለምዶ በብተና ከሚደረገው አዘራር በተሻለ ውጤታማ እንዲሆኑ ያገዛቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደሥላሴ በወቅቱ እንዳሉት፤ የምርምር ማዕከሉ በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያገዘ ነው፡፡


በዚህም በሌማት ትሩፋትና በአካባቢ ጥበቃ ሥራው ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑ አንስተዋል፡፡

በምርምር ማዕከሉ እገዛ እየተገኙ ያሉ ስኬቶችን የማስፋት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

ጉብኝቱ የምርምር ማዕከሉ ግብርናውን ለማዘመን የሚያከናውናቸው ሥራዎችን ለባለድርሻ አካላት የማሳወቅ፣ ግብዓት የማግኘትና ተሞክሮ መለዋወጥን ዓላማ ያደረገ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ (ዶ/ር) ናቸው፡፡


ማዕከሉ የስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄ፣ ተልባ፣ እንሰትና የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል ጨምሮ ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነት ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ግብርና፣ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮች እና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026