የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ማዕከላቱ በመዲናዋ የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን በማመጣጠን የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት እንዲፈጠር አስችለዋል

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡-በአዲስ አበባ የተገነቡ የንግድ ማዕከላት የምርት አቅርቦትና ፍላጎቱን በማመጣጠን የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት እንዲፈጠር ሚናቸውን እየተወጡ መሆኑን ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ ሸማችና ነጋዴውን ማገናኘት የሚያስችሉ ግዙፍ የገበያ ማዕከላት ተገንብተው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ማዕከላቱ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን ጨምሮ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በስፋት እያቀረቡ ይገኛሉ።


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ጸጋየ ደበሌ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአዲስ አበባ ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት ለመዘርጋትና የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም በመዲናዋ የተለያዩ ቦታዎች ግዙፍ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቅሰው፤ ማዕከላቱ የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

በገበያ ማዕከላቱ የሚቀርቡ ምርቶች ከ15 እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ እንዳላቸው አመልክተዋል።

ከገበያ ማዕከላቱ በተጨማሪ የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ገበያን በማረጋጋት ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በገበያ ማዕከላቱ ሲገበያዩ ያገኘናቸው ፍቅሬ ድርሻ የሚፈልጉትን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ መገብየታቸውን ተናግረዋል።

ፈቲያ አሚኑ በበኩሏ በማዕከሉ ለገበያ የቀረቡ ምርቶች ውጭ ከሚሸጡበት ዋጋ ሰፊ ልዩነት እንዳላቸው ገልጻለች።


የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶቹ ከአምራቾች በቀጥታ ለሸማቾች መቅረባቸው ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ዕድል መፍጠሩን የተናገሩት ደግሞ ደረጀ ሀይሉ ናቸው።


በገበያ ማዕከሉ ምርቶቻቸውን ከሚያቀርቡ አምራቾች መካከል ጉርሙ ጨልቀባ የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር ምርታቸውን በቀጥታ ለሸማቹ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።


በመዲናዋ አራቱም ማዕዘናት በሚገኙ የገበያ ማዕከላት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያለው ምርት እያቀረቡ መሆኑን የገለፁት አቶ ሄኖክ መንግስቱ የተባሉ አምራች ናቸው።


ሌላኛው አምራች አቶ አለማየሁ ራጎ በበኩላቸው መንግስት ለአምራቹ የመስሪያ ቦታ ማመቻቸቱ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች እንዲደርሱ ዕድል መፍጠሩን አስታውቀዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026