የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ሀብትና የሰው ሀይል በመጠቀም የህዝቡን ኑሮ የማሻሻል ተግባሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል-ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ህብትና የሰው ሀይል በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የሚከናወኑት ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) አስታወቁ።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በበጀት ዓመቱ በንቅናቄ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ከክልሉ አመራር አባላት ጋር መክረዋል።


በመድረኩ እንዳሉት፥ ያለንን የተፈጥሮ ሀብትና የሰው ሀይል በተገቢው በመጠቀም ለህዝቡ የመልማት እድል መፍጠር በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።


በገጠር ኮሪደር የተጀመሩ ስራዎችን ጥራት ማስጠበቅና ተደራሽነትን ማስፋት፣ ዘመናዊ የገጠር መንደሮችን መፍጠር፣ የከተማ ኮሪደር ልማትን አጠናከሮ ማስቀጠል ደግሞ ከትኩረት አቅጣጫዎች ዋነኞቹ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ ማድረግ፣የከተማ ግብርናና የግብይት ማዕከላትን መገንባትም ትኩረት የሚሹ መሆናቸውን አንስተው፤ በግብርናው ዘርፍም ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አጠቃቀምን በማሻሻል ዘመናዊ አሰራሮች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተናግረዋል።


በኢንዱስትሪ፣በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎችም ተሞክረው ውጤት ያመጡ ተግባራትን በአርዓያነት በመውሰድ ለመስራት ታቅዷል ብለዋል።


አክለውም፥ አመራሩ የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎችን ለመፈፀም በቅድሚያ የራሱን የስራ ባህል መቀየርና ተግባራትን በቁርጠኝነት መፈፀም ላይ ማተኮር እንዳለበትም አሳስበዋል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በበኩላቸው፥ የግብርናና ገጠር ልማት ሽግግርን ውጤታማ ለማድረግ ግብርናውን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።


ለዚህም የሚለማውን የማሳ ሽፋን ከማሳደግ ባሻገር ግብዓት አጠቃቀምን ማሳደግና ዘመናዊ አሰራርን መከተል እንደሚገባ ገልጸው፥ ሊታረስ ከሚችለው ማሳ ውስጥ 25 በመቶው በኩታ ገጠም እንደሚታረስ ተናግረዋል።


በተለይም የአፈር ማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ያለውን ክፍተት ፈጥኖ ማረም ላይ አመራሩ በልዩ ትኩረትና ቁርጠኝነት ወደ ስራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንዳሉት፥ ሁሉም አመራር ለብልፅግና የሚደረገውን ጉዞ ለማሳካት እቅዶችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም በቁጭት ወደ ተግባር መግባት አለበት ብለዋል።


ክልሉ ያለውን ሰፊ የመልማት ፀጋዎች በተገቢው ለይቶና አውቆ የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት የአመራሩ ቀዳሚ ተልዕኮ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026