የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ማንሰራራት መሰረት ጥሏል -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ማንሰራራት መሰረት መጣሉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ ተገንብተው የተጠናቀቁና በግንባታ ላይ ያሉ የተለያዩ የማምረቻ ፋብሪካዎችን ጎብኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የዘይት ፋብሪካና የአልሚ የምግብ ማቀነባበርያ ፋብሪካን መጎብኘታቸውን አንስተዋል።

በዚህም ፋብሪካዎቹ አለም አቀፍ ደረጃቸው የጠበቁ ምርቶችን በማምረት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ እንደሚገኙ መመልከታቸው ጠቁመዋል።

በተለይም ከዘይት ምርት የሚገኘውን ተረፈ ምርት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባሻገር ወደ ውጭ በመላክ የተሻለ ገቢ እየተገኘ መሆኑን አንስተዋል።

አንዳንዶቹ ወደ ግል የኢንዱስትሪ መንደርነት የሚያድጉ እንደሆኑም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጨምረው ገልፀዋል።

እንዲሁም የቢራ ገብስን የሚተካ የበቆሎ ግብዓትን የሚጠቀም ፋብሪካ መጎብኘታቸውን ገልፀው፤ ፋብሪካው በበቆሎ አምራች ገበሬዎችንና በኢንዱስትሪው መካከል ትሥሥርን የሚፈጥር፤ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች የሚተካ ነው ብለዋል።

በዚህም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥር እንደሆነ ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብታቸው የተመለከቱት የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በማምረት ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

እንዲሁም በጥቃቅንና አነስተኛ ለሰለጠኑ ባለሙያዎች ተጨማሪ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የስራ እድል መፍጠር መቻሉና የራሳቸውን ድርጅት እንዲከፍቱ እገዛ መደረጉ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ጠቅሰዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ የተመለከቷቸው የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን ብልፅግና አይቀሬነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በከተማው ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች በመገንባት ላይ መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አካባቢው ሰላማዊ መሆኑ ምርታማነት እንዲነቃቃ ማድረጉን መመልከታቸውን አስታውቀዋል።

በከተማዋና በዙሪያዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማፋጠን የክልሉና የፌዴራል መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ባለሀብቱ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ ዕድል መፍጠሩንም አስረድተዋል፡፡

እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች በማምረት ወደ ውጪ ለመላክ የሚያስችሉ አመርቂ ተግባራት መከናወናቸውን በማድነቅ ሥራዎቹን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026