የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በእንስሳት ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- በእንስሳት ሀብት ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ101ኛ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለ8ኛ ጊዜ የተከበረውን የእንስሳት ቀን በማስመልከት በአዳማ ከተማ ዛሬ የፓናል ውይይት ተካሄዷል።


በፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ፤ የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተለያዩ ኢንሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።

በተለይ በእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ፣ በመኖ ልማት፣ በእንስሳት ጤናና ደህንነት ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል።

የእንስሳት ቀኑን ከማሰብ ባለፈ የእንስሳት ሀብቱ ላይ በተለይ ወተትና የወተት ተዋፅኦ እንዲሁም የስጋ ምርት ውጤታማነት ላይ ውይይት በማካሄድ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መቀመጡን ገልጸዋል ።

ሚኒስቴሩ በእንስሳት ሀብት ውጤታማነት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ አሰራሮችና የህግ ማዕቀፎችን ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።

ለዚህም የእንስሳት ጤና ስትራቴጂና የማስፈፀሚያ ስልቶች በመቅረፅ በተለይ የእንስሳት ሀብቱን በዘመናዊ መንገድ ለማልማት የሚያግዙ ስራዎችን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እየሰራ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ እንስሳት ሀኪሞች ማህበር ፕሬዚዳንት ቦጂያ ሂንደቡ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የእንስሳት ጤናና ደህንነት አዋጅ መውጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም የእንስሳት ጤና ሙያተኞች በዕውቀታቸው ዘርፉን እንዲደግፉ እድል የሰጠ ነው ብለዋል።

በተለይ በእንስሳት ጤና አጠባበቅ ላይ የተሻለ ሙያዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፤ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የሀብቱን ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

ባለድርሻ አካላት በእንስሳት ጤና አጠባበቅና ሀብትን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀረፁ ስትራቴጂዎች፣ አሰራሮችና የህግ ማዕቀፎች ውጤታማ እንዲሆኑ በንቃት ሊሳተፉ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025