የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በእንስሳት ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- በእንስሳት ሀብት ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ101ኛ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለ8ኛ ጊዜ የተከበረውን የእንስሳት ቀን በማስመልከት በአዳማ ከተማ ዛሬ የፓናል ውይይት ተካሄዷል።


በፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ፤ የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተለያዩ ኢንሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።

በተለይ በእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ፣ በመኖ ልማት፣ በእንስሳት ጤናና ደህንነት ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል።

የእንስሳት ቀኑን ከማሰብ ባለፈ የእንስሳት ሀብቱ ላይ በተለይ ወተትና የወተት ተዋፅኦ እንዲሁም የስጋ ምርት ውጤታማነት ላይ ውይይት በማካሄድ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መቀመጡን ገልጸዋል ።

ሚኒስቴሩ በእንስሳት ሀብት ውጤታማነት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ አሰራሮችና የህግ ማዕቀፎችን ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።

ለዚህም የእንስሳት ጤና ስትራቴጂና የማስፈፀሚያ ስልቶች በመቅረፅ በተለይ የእንስሳት ሀብቱን በዘመናዊ መንገድ ለማልማት የሚያግዙ ስራዎችን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እየሰራ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ እንስሳት ሀኪሞች ማህበር ፕሬዚዳንት ቦጂያ ሂንደቡ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የእንስሳት ጤናና ደህንነት አዋጅ መውጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም የእንስሳት ጤና ሙያተኞች በዕውቀታቸው ዘርፉን እንዲደግፉ እድል የሰጠ ነው ብለዋል።

በተለይ በእንስሳት ጤና አጠባበቅ ላይ የተሻለ ሙያዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፤ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የሀብቱን ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

ባለድርሻ አካላት በእንስሳት ጤና አጠባበቅና ሀብትን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀረፁ ስትራቴጂዎች፣ አሰራሮችና የህግ ማዕቀፎች ውጤታማ እንዲሆኑ በንቃት ሊሳተፉ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026