🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የቅርስ ጥገና፣ እንክብካቤና የሙዝየም ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ መልካሙ ፀጋየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉን በማልማትና በማስተዋወቅ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።
በተለይም ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የመስህብ ሃብቶች ልማት፣ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
በክልሉ 437 ሚሊዮን ብር ተመድቦ የሙዚየሞች ግንባታና የቅርሶች ጥገና እየተካሄደ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በግንባታ ላይ ካሉ ሙዝየሞች መካከል በባህርዳር የክልሉ ህዝብ ሙዝየም፣ በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ የጀነራል ሀይሉ ከበደ መታሰቢያ ሙዝየም፣ በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ የይስማህ ንጉስ ሙዝየም እንደሚገኙበት ለአብነት ጠቅሰዋል።
በዚህ አመትም የ27 ቅርሶች ጥገና ስራ እንደሚጠናቀቅ ጠቁመው በማእከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ ባህሪ ግንብና ድብሳን ግንብ እንደሚገኙበት አመልክተዋል።
የክልሉን የቱሪስት መስህቦች የማልማትና ቅርሶችን የመጠበቅ ተግባራትም የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ቱሪስቶችን ፍሰት ከማሳደጉ ባሻገር ቆይታቸውን ለማራዘም የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራው የቱሪዝም ዘርፉን ከማሳደግ በለፈ ትውልዱ ታሪክን በመረዳት ለልማትና ለሰላም ይበልጥ እንዲተጋ የራሱ ድርሻ እንዳለውም ገልፀዋል።
በክልሉ የቅርስ ጥበቃ ስራው በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025