🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የቅርስ ጥገና፣ እንክብካቤና የሙዝየም ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ መልካሙ ፀጋየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉን በማልማትና በማስተዋወቅ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።
በተለይም ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የመስህብ ሃብቶች ልማት፣ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
በክልሉ 437 ሚሊዮን ብር ተመድቦ የሙዚየሞች ግንባታና የቅርሶች ጥገና እየተካሄደ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በግንባታ ላይ ካሉ ሙዝየሞች መካከል በባህርዳር የክልሉ ህዝብ ሙዝየም፣ በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ የጀነራል ሀይሉ ከበደ መታሰቢያ ሙዝየም፣ በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ የይስማህ ንጉስ ሙዝየም እንደሚገኙበት ለአብነት ጠቅሰዋል።
በዚህ አመትም የ27 ቅርሶች ጥገና ስራ እንደሚጠናቀቅ ጠቁመው በማእከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ ባህሪ ግንብና ድብሳን ግንብ እንደሚገኙበት አመልክተዋል።
የክልሉን የቱሪስት መስህቦች የማልማትና ቅርሶችን የመጠበቅ ተግባራትም የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ቱሪስቶችን ፍሰት ከማሳደጉ ባሻገር ቆይታቸውን ለማራዘም የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራው የቱሪዝም ዘርፉን ከማሳደግ በለፈ ትውልዱ ታሪክን በመረዳት ለልማትና ለሰላም ይበልጥ እንዲተጋ የራሱ ድርሻ እንዳለውም ገልፀዋል።
በክልሉ የቅርስ ጥበቃ ስራው በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026