🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የቅርስ ጥገና፣ እንክብካቤና የሙዝየም ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ መልካሙ ፀጋየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉን በማልማትና በማስተዋወቅ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።
በተለይም ለቱሪዝም ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት የመስህብ ሃብቶች ልማት፣ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
በክልሉ 437 ሚሊዮን ብር ተመድቦ የሙዚየሞች ግንባታና የቅርሶች ጥገና እየተካሄደ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በግንባታ ላይ ካሉ ሙዝየሞች መካከል በባህርዳር የክልሉ ህዝብ ሙዝየም፣ በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ የጀነራል ሀይሉ ከበደ መታሰቢያ ሙዝየም፣ በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ የይስማህ ንጉስ ሙዝየም እንደሚገኙበት ለአብነት ጠቅሰዋል።
በዚህ አመትም የ27 ቅርሶች ጥገና ስራ እንደሚጠናቀቅ ጠቁመው በማእከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ ባህሪ ግንብና ድብሳን ግንብ እንደሚገኙበት አመልክተዋል።
የክልሉን የቱሪስት መስህቦች የማልማትና ቅርሶችን የመጠበቅ ተግባራትም የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ቱሪስቶችን ፍሰት ከማሳደጉ ባሻገር ቆይታቸውን ለማራዘም የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራው የቱሪዝም ዘርፉን ከማሳደግ በለፈ ትውልዱ ታሪክን በመረዳት ለልማትና ለሰላም ይበልጥ እንዲተጋ የራሱ ድርሻ እንዳለውም ገልፀዋል።
በክልሉ የቅርስ ጥበቃ ስራው በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026