የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአፄ ፋሲል አብያተ መንግስት የጉብኝት ስርዓትን ለማዘመን እየተሰራ ነው

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ሕዳር 17/2018 (ኢዜአ)፦ በጎንደር የአፄ ፋሲል አብያተ መንግስት የጉብኝት ስርዓትን የማዘመን ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የአብያተ መንግስቱን የጉብኝት ስርዓት ለማዘመን የመግቢያ ቲኬት የዲጂታል አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀመርም ተመልክቷል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፡ የጎንደር አብያተ መንግስትን የጉብኝት ስርዓት ለማዘመን አዳዲስ የጉብኝት ፓኬጆችን ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡


በዚህም የሀገር ውስጥም ሆነ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ሲስተናገዱበት የቆየውን የወረቀት የመግቢያ ቲኬት በማስቀረት ቀልጣፋና ዘመናዊ የዲጂታል ትኬት አገልግሎት በቅርቡ ይጀመራል ብለዋል፡፡

የዲጂታል ትኬት አገልግሎቱን ለማስጀመርም ቢሮው ከክልሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመሆን ሶፍትዌር የማልማት ስራውን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

የዲጂታል ትኬት አገልግሎቱን በመጪው የጥምቀት በዓል ለማስጀመር መታቀዱን የጠቆሙት አቶ መልካሙ ቱሪስቶች በፈለጉበት ሰዓትና ጊዜ አስቀድመው በኦን ላይን ቲኬት መቁረጥ እንዲችሉ ያግዛል ብለዋል፡፡


ለአብያተ መንግስቱ በተደረገው እድሳትም የመብራት ቴክኖሎጂና የደህንነት ካሜራዎች የተገጠሙ በመሆኑ ከቀን በተጨማሪ ምሽት ላይ ለማስጎብኘት አዲስ የጉብኝት ፓኬጅ ማዘጋጀት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡

ከአዳዲስ የጉብኝት ፓኬጆች መካከልም በቢሮውና በቱሪዝም ሚኒስቴር የጋራ ትብብር በቅርቡ በይፋ የተጀመረው "ህይወት በአብያተ መንግስት ትዕይንት" ፕሮጀክት ቀጣይ እንዲሆንም ይደረጋል ብለዋል።


የነገስታቱን የቀደመ ታሪክና ክዋኔ ወደ ኋላ በምልሰት በማስታወስ የሚቀርበው የኪነ ጥበብ ዝግጅት የቱሪስቶችን ቆይታ በማራዘም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።

መንግስት ለቱሪዝም ልማቱ በሰጠው ልዩ ትኩረት የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት ሙሉ እድሳት ከተደረገለት በኋላ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ለጉብኝት ክፍት መደረጉ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026