🔇Unmute
አምቦ ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ አልፎ አኮኖሚያዊ አቅማቸውን ለማሳደግ እንዳገዛቸው የአምቦ ከተማ ዙሪያ አርሶ አደሮች ተናገሩ ።
የአምቦ ከተማ ዙሪያ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዘር የመሸፈን የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ የአምቦ ከተማ ዙሪያ አርሶአደሮች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የዝናብ ወቅትን ጠብቀው በአመት አንድ ጊዜ የሚያለሙትን ስርአት በመቀየር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን ተናግረዋል።
አርሶአደር አቶ ተሾመ ለገሠ እንዳሉት፤ ከዚህ በፊት የመኽር ሰብላቸውን ከሰበሰቡ በኃላ በበጋው ወቅት መሬታቸው ከልማት ውጭ እንደሚሆን አስታውሰዋል።

ባለፉት አመታት ግን በበጋው ወቅት ከልማት ውጪ የሆነውን መሬታቸውን በበጋ ስንዴ መስኖ ማልማት የሚችሉበትን ግንዛቤ ከግብርና ባለሙያዎች በማግኘታቸው ወደ ተግባር እንደገቡ ገልጸዋል፡፡
ለዘንድሮው የበጋ ስንዴ መስኖ ልማት መሬታቸውን ደጋግመው ማረሳቸውንና ምርጥ ዘርና ማዳበርያ በወቅቱ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
ሌላው አርሶ አደር መለሰ ታምሩ በበኩላቸው፤ በመኽር ወቅት ያለሙትን የበቆሎ ሰብል በማንሳት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል።

በዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱ ገቢያቸውን ማሳደጉንና የምግብ ዋስትናቸውን ማረጋገጥ መቻሉን አስረድተዋል።
ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱ ያገኙትን ጥቅም ለሌሎች አርሶ አደሮች እያካፈሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በከተማው የበጋ መስኖ ስንዴ እና አትክልትና ፍራፍሬን በ120 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የተናገሩት ደግሞ የአምቦ ከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ ተወካይ አቶ ታከለ ኩምሳ ናቸው፡፡

የከተማዋን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በመኽር ወቅት ብቻ መስራቱ በቂ ባለመሆኑ የበጋ መስኖ ስንዴ፣ አትክልትና ፍራፍሬዎችን የማልማቱ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንና የበጋ መስኖ የስንዴ ልማቱ በዘር የመሸፈን መርሃ ግብሩ ዛሬ በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል ፡፡
የአምቦ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ፤ በበጋ መስኖ ስንዴ ዘርን ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት የአምቦ ከተማ ግብርና የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ አልፎ ለከተማዋ እድገት አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

አርሶ አደሩ ዝናብን ጠብቆ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ሰብል የሚያመርትበትን የስራ ባህል ጭምር መቀየሩን አክለዋል።
በከተማዋ እየተለመደ የመጣው የበጋ መስኖ የስንዴ፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች ልማት የነዋሪውን የተመጣጠነ ምግብ እቅርቦት ማሳደጉን ገልጸዋል።
የበጋ መስኖ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግም የግብአትና የባለሙያ ድጋፍና ክትትል መጠናከሩን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025