🔇Unmute
ጎንደር፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብን የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ ወቅታዊ አጀንዳ ነው ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ፡፡
ትውልዱ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ሲቆጭ መቆየቱና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ፈጣን ምላሽ እንዲገኝም መጠየቁ አልቀረም።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት በጎንደር የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብ አጀንዳ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የአመራር አባል ካሳ በለጠ፤ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ የተደረገበት አካሄድ ሀገሪቱን ለማዳከም የተሸረበ ተግባር ነው ብለዋል።
የባህር በር ጥያቄው የሀገርን ጥቅም ያስቀደመና የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
የባህር በር ጥያቄ የመላ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተገኑ ደረጀ ናቸው።
የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ መኮንን ብርሃን የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ወቅታዊና ህዝባዊ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ከ30 ዓመታት በላይ ከቀይ ባህር ርቃ ቆይታ ዳግም ለመመለስ በምትችልበት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ሲሉም አስረድተዋል፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026