🔇Unmute
ጎንደር፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብን የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ ወቅታዊ አጀንዳ ነው ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ፡፡
ትውልዱ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ሲቆጭ መቆየቱና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ፈጣን ምላሽ እንዲገኝም መጠየቁ አልቀረም።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት በጎንደር የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብ አጀንዳ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የአመራር አባል ካሳ በለጠ፤ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ የተደረገበት አካሄድ ሀገሪቱን ለማዳከም የተሸረበ ተግባር ነው ብለዋል።
የባህር በር ጥያቄው የሀገርን ጥቅም ያስቀደመና የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
የባህር በር ጥያቄ የመላ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተገኑ ደረጀ ናቸው።
የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ መኮንን ብርሃን የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ወቅታዊና ህዝባዊ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ከ30 ዓመታት በላይ ከቀይ ባህር ርቃ ቆይታ ዳግም ለመመለስ በምትችልበት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ሲሉም አስረድተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025