🔇Unmute
ጎንደር፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብን የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ ወቅታዊ አጀንዳ ነው ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ፡፡
ትውልዱ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ሲቆጭ መቆየቱና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ፈጣን ምላሽ እንዲገኝም መጠየቁ አልቀረም።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት በጎንደር የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ የመላው ህዝብ አጀንዳ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የአመራር አባል ካሳ በለጠ፤ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ የተደረገበት አካሄድ ሀገሪቱን ለማዳከም የተሸረበ ተግባር ነው ብለዋል።
የባህር በር ጥያቄው የሀገርን ጥቅም ያስቀደመና የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
የባህር በር ጥያቄ የመላ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተገኑ ደረጀ ናቸው።
የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ መኮንን ብርሃን የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ወቅታዊና ህዝባዊ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ከ30 ዓመታት በላይ ከቀይ ባህር ርቃ ቆይታ ዳግም ለመመለስ በምትችልበት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ሲሉም አስረድተዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026