🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ሰብል በሚሰበሰብበትና ምርት በሚቀመጥበት ወቅት ብክነት እንዳይኖር አርሶ አደሩ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አሳሰበ።
በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ታገል ታምሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በ2017/18 የመኸር ወቅት 371 ሺህ 975 ሔክታር የእርሻ መሬት በዘር መሸፈኑን እና ከ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በዘር ከተሸፈነው 85 ሺህ 568 ሔክታሩ በ1 ሺህ 723 ክላስተሮች በተደራጁ አርሶ አደሮች መልማቱን አስረድተዋል።
አሁን ላይ በሜካናይዜሽን እና በሰው ኃይል የደረሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ሥራ በትጋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው ሂደትም ከ133 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህም ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አረጋግጠዋል።
በመኸሩ ወቅት ዋናዋና የምግብ ሰብሎች የሚባሉት ጤፍ፣ ስንዴ፣ ሩዝ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ማሾ እና ሌሎችም በስፋት መልማታቸውን አብራርተዋል።
ድንገት በሚጥል ዝናብ ምክንያት የምርት መበላሸት እንዳይኖር የደረሱ ሰብሎችን ሁሉንም አማራጭ በመጠቀም በፍጥነትና በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በሌላ በኩል የተሰበሰበ ምርትን በደረቅ ቦታ በማስቀመጥ የምርት ብክነት እንዳይኖር ጥንቃቄ እንዲደረግ መክረዋል።
የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ ሙያዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026