🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ሰብል በሚሰበሰብበትና ምርት በሚቀመጥበት ወቅት ብክነት እንዳይኖር አርሶ አደሩ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አሳሰበ።
በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ታገል ታምሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በ2017/18 የመኸር ወቅት 371 ሺህ 975 ሔክታር የእርሻ መሬት በዘር መሸፈኑን እና ከ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በዘር ከተሸፈነው 85 ሺህ 568 ሔክታሩ በ1 ሺህ 723 ክላስተሮች በተደራጁ አርሶ አደሮች መልማቱን አስረድተዋል።
አሁን ላይ በሜካናይዜሽን እና በሰው ኃይል የደረሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ሥራ በትጋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው ሂደትም ከ133 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህም ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አረጋግጠዋል።
በመኸሩ ወቅት ዋናዋና የምግብ ሰብሎች የሚባሉት ጤፍ፣ ስንዴ፣ ሩዝ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ማሾ እና ሌሎችም በስፋት መልማታቸውን አብራርተዋል።
ድንገት በሚጥል ዝናብ ምክንያት የምርት መበላሸት እንዳይኖር የደረሱ ሰብሎችን ሁሉንም አማራጭ በመጠቀም በፍጥነትና በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በሌላ በኩል የተሰበሰበ ምርትን በደረቅ ቦታ በማስቀመጥ የምርት ብክነት እንዳይኖር ጥንቃቄ እንዲደረግ መክረዋል።
የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ ሙያዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026