የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ሰብል በሚሰበሰብበትና በሚከማችበት ወቅት ብክነት እንዳይኖር ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ሰብል በሚሰበሰብበትና ምርት በሚቀመጥበት ወቅት ብክነት እንዳይኖር አርሶ አደሩ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አሳሰበ።

በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ታገል ታምሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በ2017/18 የመኸር ወቅት 371 ሺህ 975 ሔክታር የእርሻ መሬት በዘር መሸፈኑን እና ከ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በዘር ከተሸፈነው 85 ሺህ 568 ሔክታሩ በ1 ሺህ 723 ክላስተሮች በተደራጁ አርሶ አደሮች መልማቱን አስረድተዋል።

አሁን ላይ በሜካናይዜሽን እና በሰው ኃይል የደረሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ሥራ በትጋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።


እስካሁን ባለው ሂደትም ከ133 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህም ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አረጋግጠዋል።

በመኸሩ ወቅት ዋናዋና የምግብ ሰብሎች የሚባሉት ጤፍ፣ ስንዴ፣ ሩዝ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ማሾ እና ሌሎችም በስፋት መልማታቸውን አብራርተዋል።

ድንገት በሚጥል ዝናብ ምክንያት የምርት መበላሸት እንዳይኖር የደረሱ ሰብሎችን ሁሉንም አማራጭ በመጠቀም በፍጥነትና በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባም አሳስበዋል።


በሌላ በኩል የተሰበሰበ ምርትን በደረቅ ቦታ በማስቀመጥ የምርት ብክነት እንዳይኖር ጥንቃቄ እንዲደረግ መክረዋል።

የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ ሙያዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025