🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ሰብል በሚሰበሰብበትና ምርት በሚቀመጥበት ወቅት ብክነት እንዳይኖር አርሶ አደሩ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አሳሰበ።
በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ታገል ታምሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በ2017/18 የመኸር ወቅት 371 ሺህ 975 ሔክታር የእርሻ መሬት በዘር መሸፈኑን እና ከ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በዘር ከተሸፈነው 85 ሺህ 568 ሔክታሩ በ1 ሺህ 723 ክላስተሮች በተደራጁ አርሶ አደሮች መልማቱን አስረድተዋል።
አሁን ላይ በሜካናይዜሽን እና በሰው ኃይል የደረሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ሥራ በትጋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው ሂደትም ከ133 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህም ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አረጋግጠዋል።
በመኸሩ ወቅት ዋናዋና የምግብ ሰብሎች የሚባሉት ጤፍ፣ ስንዴ፣ ሩዝ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ ማሾ እና ሌሎችም በስፋት መልማታቸውን አብራርተዋል።
ድንገት በሚጥል ዝናብ ምክንያት የምርት መበላሸት እንዳይኖር የደረሱ ሰብሎችን ሁሉንም አማራጭ በመጠቀም በፍጥነትና በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በሌላ በኩል የተሰበሰበ ምርትን በደረቅ ቦታ በማስቀመጥ የምርት ብክነት እንዳይኖር ጥንቃቄ እንዲደረግ መክረዋል።
የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ ሙያዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026