የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ሕዝብን በማስተባበር እየተከናወኑ ያሉ ሐረርን የማስዋብ ሥራዎች …

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ሕዝብን በማስተባበር እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎች ሐረር ቀደምት ስልጣኔዋን በሚመጥን ደረጃ ላይ እንድትገኝ እያስቻሉ መሆኑን የሐረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

ሐረር ከተማ የዘመናዊ ከተሜነትን እሳቤ ቀድሞ በመተግበር ከሚጠቀሱት ግንባር ቀደሞች መካከል መሆኗን የሐረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሔኖክ ሙሉነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አውስተዋል።

ይሁን እንጅ በተለይም ከለውጡ መንግሥት በፊት ለውጥን እንደናፈቀች የሕዝቦቿም የመልማት ፍላጎት ከምኞት መሻገር ሳይችል መቆየቱን በቁጭት አንስተዋል።


ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ግን የአመራሩ ቁርጠኝነት እና ሕዝቡ በልማቱ የመሳተፍ ዐቅም በይበልጥ በማደጉ ከተማዋን የማዘመን ተግባራት አርአያ በሚሆን መልኩ እየተሠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ለአብነትም፤ ከኮሪደር ልማቱ ጅማሮ ማግስት የክልሉ መንግሥት የአካባቢያዊ ፀጋዎችንና ዐቅሞችን መነሻ ያደረጉ ውጤታማ ሥራዎችን በተቀናጀና በተናበበ መልኩ እያከናወነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

ይህን ተከትሎም በአነስተኛ ወጪ፣በላቀ የአመራር ጥበብና ቁርጠኝነት ሕዝብን በማስተባበር እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎች የከተማዋን ታሪክና ቀደምት ሥልጣኔ በሚመጥን ደረጃ እንድትገኝ የሚያስችሉ ናቸው።

ሐረር ዛሬ በይበልጥ መነቃቃቷን የገለጹት ኃላፊው፤ ወደ ኋላ የቀረችባቸው ዓመታትን ለመካስ በሚያስችል ደረጃ ቀንና ሌሊት እየተሠራ ነው ብለዋል።

አመራሩም ለሥራዎቹ ጥራትና ፍጥነት በላቀ ኃላፊነት ክትትል እያደረገ እንደሚገኝም አክለዋል።

የተሽከርካሪና የብስክሌት እንዲሁም የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አረንጓዴ ስፍራንና ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶችን ባካተተ መልኩ እየተሠራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ውብና ማራኪ እንድትሆን አስችሏል ብለዋል።

የክልሉ ሕዝብና መንግሥት እጅ ለእጅ በመያያዝ እያኖሩት የሚገኘው አዲስ የስኬት ታሪክም የከተማውን ውበት የገለጠ ብቻ ሳይሆን፤ በክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪዝም ዐቅም ለመጠቀም ያገዘ ነው ብለዋል።

በከተማው በየአካባቢው እውን የተደረጉና እየተደረጉ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎችም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉንም ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ከፅዳት መጓደል ጋር በተያያዘ ሲስተዋሉ የቆዩ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድም ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን አረጋግጠዋል።

የሐረርን ከፍታ ሲመኙ የነበሩ የከተማው ነዋሪዎችም እያደረች እየፈካች በምትገኘ ከተማቸው ልማት ላይ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ከተሞች ብቸኛዋ የዓለም ቅርስ ከተሞች ድርጅት አባል በሆነችው ሐረር ከተማ ቀን ከሌሊት በመሥራት በአጭር ጊዜ የተገኘው ውጤትና የተመዘገበው ስኬትም የሥራ ባህልን የቀየረና የይቻላል መንፈስን ያሰረፀ ሆኗል ነው ያሉት።

የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በሚያሳድግ መልኩ እየተሠሩ የሚገኙ ሥራዎችና የታዩ ውጤቶችም የሐረርን ገናናነት ዳግም እውን ማድረግ እንደሚቻል አመላካች መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል ኃላፊው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025