🔇Unmute
ሐረር ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን በ20 ወረዳዎች ሙዝ በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።
በኦሮሚያ ክልል ባለው ምቹ ሥነ ምህዳር፣ ተስማሚ የአየር ንብረትና ሰፊ የሚለማ መሬት ልክ አልምቶ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተለያዩ የግብርና ልማት ኢንሼቲቮች ተቀርጸው ወደ ተግባር ገብተዋል።
ከእነዚህ አዳዲስ ኢንሼቲቮች መካከል የሻይ ቅጠል፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ሩዝ፣ የበጋ መስኖ ስንዴ እና ሙዝ ልማት ተጠቃሾች ናቸው።
ምሥራቅ ሐረርጌ ዞንም የክልሉን የልማት ኢንሼቲቮች ተቀብለው ተግባራዊ ካደረጉ ዞኖች አንዱ ነው።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሐመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ እንደ ምስራቅ ሐረርጌ ዞን በኢንሼቲቭ ከሚከናወኑና ትልቅ ለውጥ እያስገኙ ከሚገኙት የልማት መስኮች አንዱ የሙዝ ምርት ነው።
በ2011 ዓ.ም በስድስት ወረዳዎች የተጀመረው የሙዝ ልማት ኢንሼቲቭ በአሁኑ ወቅት በ20 ወረዳዎች ላይ በኩታገጠም እየለማ ይገኛል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ አቮካዶ፣ ብርትኳንና የመሳሰሉት ፍራፍሬዎች እየለሙና ሌሎች የሌማት ትሩፋት ተግባራትም እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
በልማት ስራው እየተሳተፉ የሚገኙ የተደራጁ ወጣቶችና አርሶ አደሮችም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
የሙዝ ምርቱ ከዞኑ ባለፈ ለድሬዳዋ፣ ሐረርና ጅግጅጋ አካባቢዎች እንዲሁም ጅቡቲን ጨምሮ ለጎረቤት አገራት ገበያ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው የሙዝ ልማቱን የማስፋት ስራ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።

በዞኑ ሙዝ አብቃይ ከሆኑ ወረዳዎች መካከል የጉርሱም ወረዳ አንዱ ሲሆን በወረዳው የሃሮ ባቴ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ንዋይ ታዬ ፤ በቀበሌው በ6 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የተጀመረው የሙዝ ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 26 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ከፍ ብሎ በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀበሌው በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውና አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደረገው የሙዝ ዝርያ የተሻለ ምርት የሚሰጥ መሆኑን በመረዳት የማስፋት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በወረዳው የሙዝና አቮካዶ ልማት ኢንሼቲቭ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ያሉት ደግሞ በጉርሱም ወረዳ የቡናና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ አቶ ሶሬሳ ንጉሳ ናቸው።

በተለይ በወረዳው 1 ሺህ 472 አርሶ አደሮች ሙዝን በኩታገጠም እያለሙና ተጠቃሚነታቸውንም እያረጋገጡ እንደሚገኙ ጠቁመው የሙዝ ልማትን የማጎልበት ስራው እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በጉርሱም ወረዳ የሃሮ ባቴ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር ከድር አብዱላሂ፣ በኩታገጠም ሙዝ እያመረቱበት የሚገኘው መሬት ቀደም ሲል ምንም ጥቅም ሳይሰጥ የቆየ መሆኑን አንስተዋል።

ባለፈው ዓመት ባከናወኑት ስራ 2 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘታቸውን እና ዘንድሮ ከአምናው ሶስት እጥፍ ገቢ የሚያስገኝ የሙዝ ልማት ማከናወናቸውን ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026