🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ ያስመዘገበቻቸው ጉልህ መሻሻሎች የሚደነቁ መሆናቸውን የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል ገለጹ።
የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የዓለም አቀፉ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስብሰባው በኢትዮጵያ መካሄዱ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ጉልህ የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች ያለች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ይህም የድህነት መጠን እንዲቀንስ እና እንደ ጤናና ትምህርት ባሉ ማህበራዊ ዘርፎች ላይ መሻሻሎችን ማምጣቱን ተናግረዋል።

ሀገሪቱ በአስደናቂ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ጉዞ ላይ ናት ያሉት ዋና ጸሐፊው ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ መሻሻል መኖሩን ጠቁመዋል።
በዓለም ዙሪያ ሠራተኞች እየተጋፈጧቸው ያሉ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮችን ለመፍታት ጠንካራና ድንበር ተሻጋሪ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በበኩላቸው በኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ የኢንዱስትሪ አቅምን ለማስፋት፣ ታዳሽ ኃይልን ለማስፋፋት እና ብሔራዊ ኢኮኖሚን ለማጠናከር በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህም የሠራተኛውን ማህበረሰብና የአጠቃላይ ህዝቡን የኑሮ ሁኔታ የሚቀይሩ እንዲሁም ለሚቀጥለው ትውልድ ምቹ የሥራና የኑሮ ምህዳርን ለመፍጠር መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
የሠራተኛ ገበያው እየተለወጠ እና አዳዲስ የሥራ ዓይነቶች እየተፈጠሩ ሲመጡ የሠራተኛ ማኅበራት የሚገጥሟቸው ፈተናዎች ለመሻገር የጋራ እና የተቀናጀ መፍትሄዎችን እንደሚሹም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026