የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ ያስመዘገበቻቸው ጉልህ መሻሻሎች የሚደነቁ ናቸው - ዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ ያስመዘገበቻቸው ጉልህ መሻሻሎች የሚደነቁ መሆናቸውን የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል ገለጹ።

የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


የዓለም አቀፉ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስብሰባው በኢትዮጵያ መካሄዱ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።

ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ጉልህ የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች ያለች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ይህም የድህነት መጠን እንዲቀንስ እና እንደ ጤናና ትምህርት ባሉ ማህበራዊ ዘርፎች ላይ መሻሻሎችን ማምጣቱን ተናግረዋል።


ሀገሪቱ በአስደናቂ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ጉዞ ላይ ናት ያሉት ዋና ጸሐፊው ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ መሻሻል መኖሩን ጠቁመዋል።

በዓለም ዙሪያ ሠራተኞች እየተጋፈጧቸው ያሉ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮችን ለመፍታት ጠንካራና ድንበር ተሻጋሪ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በበኩላቸው በኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ የኢንዱስትሪ አቅምን ለማስፋት፣ ታዳሽ ኃይልን ለማስፋፋት እና ብሔራዊ ኢኮኖሚን ለማጠናከር በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የሠራተኛውን ማህበረሰብና የአጠቃላይ ህዝቡን የኑሮ ሁኔታ የሚቀይሩ እንዲሁም ለሚቀጥለው ትውልድ ምቹ የሥራና የኑሮ ምህዳርን ለመፍጠር መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

የሠራተኛ ገበያው እየተለወጠ እና አዳዲስ የሥራ ዓይነቶች እየተፈጠሩ ሲመጡ የሠራተኛ ማኅበራት የሚገጥሟቸው ፈተናዎች ለመሻገር የጋራ እና የተቀናጀ መፍትሄዎችን እንደሚሹም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026