የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ ያስመዘገበቻቸው ጉልህ መሻሻሎች የሚደነቁ ናቸው - ዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ ያስመዘገበቻቸው ጉልህ መሻሻሎች የሚደነቁ መሆናቸውን የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል ገለጹ።

የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


የዓለም አቀፉ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሐፊ ሉክ ትራያንግል በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስብሰባው በኢትዮጵያ መካሄዱ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።

ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ጉልህ የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች ያለች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ይህም የድህነት መጠን እንዲቀንስ እና እንደ ጤናና ትምህርት ባሉ ማህበራዊ ዘርፎች ላይ መሻሻሎችን ማምጣቱን ተናግረዋል።


ሀገሪቱ በአስደናቂ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ጉዞ ላይ ናት ያሉት ዋና ጸሐፊው ከሠራተኛ ማኅበራት መብቶች ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ መሻሻል መኖሩን ጠቁመዋል።

በዓለም ዙሪያ ሠራተኞች እየተጋፈጧቸው ያሉ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮችን ለመፍታት ጠንካራና ድንበር ተሻጋሪ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በበኩላቸው በኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ የኢንዱስትሪ አቅምን ለማስፋት፣ ታዳሽ ኃይልን ለማስፋፋት እና ብሔራዊ ኢኮኖሚን ለማጠናከር በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የሠራተኛውን ማህበረሰብና የአጠቃላይ ህዝቡን የኑሮ ሁኔታ የሚቀይሩ እንዲሁም ለሚቀጥለው ትውልድ ምቹ የሥራና የኑሮ ምህዳርን ለመፍጠር መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

የሠራተኛ ገበያው እየተለወጠ እና አዳዲስ የሥራ ዓይነቶች እየተፈጠሩ ሲመጡ የሠራተኛ ማኅበራት የሚገጥሟቸው ፈተናዎች ለመሻገር የጋራ እና የተቀናጀ መፍትሄዎችን እንደሚሹም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026