የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የጅማ ከተማ የኮሪደር  ልማት የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር አስችሏል

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡-የጅማ ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ እና ማራኪ በማድረጉ የጎብኚዎች ቁጥር መጨመሩን የከተማው ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የኮሪደር ልማት በስፋት ከተካሄደባቸው ከተሞች መካካል ጅማ ተጠቃሽ ስትሆን በከተማው የተሰራው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከማስዋብ ባለፈ በርካታ እድሎች ይዞ የመጣ መሆኑ ተመልክቷል።


ከእድሎቹ መካከል በከተማው የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ አንዱ ሲሆን በተለያዩ ዘርፎች የተፈጠረው የስራ እድልም ይጠቀሳል።

የጅማ ከተማ የቱሪዝም ጽህፈት ቤት ሀላፊ ሮዚ ዛኪር እንደተናገሩት፤ በጅማ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪ ብቻ ሳይሆን ለጎብኚዎችም ምቹ አድርጓታል።


በኮሪደር ልማት ስራው የአገር ውስጥ እና የውጪ አገር ጎብኚዎች ቁጥር መጨመሩን ጠቅሰው ባለፈው ዓመት ከ1 ሺህ በላይ የውጪ አገር ጎብኚዎች ከተማዋን ጎብኝተዋል ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በርካታ የአገር ውስጥ እና የውጪ ጎብኝዎች ጅማን እየጎበኙ መሆኑን ጠቁመው ጎብኚዎቹ በዋናነት የአባጅፋር ቤተመንግስት እና የቦዬ ሀይቅን እየጎበኙ ነው ብለዋል።


በከተማዋ የኮሪደር ልማት ስራ የጎብኚዎች ቁጥር ከመጨመር ባለፈ ጅማን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን እድል እየፈጠረላት መሆኑንም አስረድተዋል።


በከተማዋ በተገነባው የኮሪደር ልማት የጎዳና ላይ ፎቶ የስራ እድል የተፈጠረላቸው የከተማው ወጣቶችም ኮሪደር ልማቱ ገቢ እንደፈጠረላቸውም ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በከተማዋ አደባባዮችና ጎዳናዎች በኮሪደር ልማቱ ላይ የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎችን ፎቶ በማንሳት ገቢ እያገኙ ይገኛሉ።


በከተማዋ ኮሪደር ልማት አማካኝነት በተፈጠረላቸው የስራ እድል ደስተኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በጅማ ከተማ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በዋና ዋና መንገድ ዳር የቡና መሸጫ ቤቶች፣ ፈጣን ምግቦች መሸጫ እና የእንጨት ውጤቶች መሸጫ ሱቆች በብዛት ስራ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025