የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የጅማ ከተማ የኮሪደር  ልማት የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር አስችሏል

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡-የጅማ ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ እና ማራኪ በማድረጉ የጎብኚዎች ቁጥር መጨመሩን የከተማው ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የኮሪደር ልማት በስፋት ከተካሄደባቸው ከተሞች መካካል ጅማ ተጠቃሽ ስትሆን በከተማው የተሰራው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከማስዋብ ባለፈ በርካታ እድሎች ይዞ የመጣ መሆኑ ተመልክቷል።


ከእድሎቹ መካከል በከተማው የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ አንዱ ሲሆን በተለያዩ ዘርፎች የተፈጠረው የስራ እድልም ይጠቀሳል።

የጅማ ከተማ የቱሪዝም ጽህፈት ቤት ሀላፊ ሮዚ ዛኪር እንደተናገሩት፤ በጅማ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪ ብቻ ሳይሆን ለጎብኚዎችም ምቹ አድርጓታል።


በኮሪደር ልማት ስራው የአገር ውስጥ እና የውጪ አገር ጎብኚዎች ቁጥር መጨመሩን ጠቅሰው ባለፈው ዓመት ከ1 ሺህ በላይ የውጪ አገር ጎብኚዎች ከተማዋን ጎብኝተዋል ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በርካታ የአገር ውስጥ እና የውጪ ጎብኝዎች ጅማን እየጎበኙ መሆኑን ጠቁመው ጎብኚዎቹ በዋናነት የአባጅፋር ቤተመንግስት እና የቦዬ ሀይቅን እየጎበኙ ነው ብለዋል።


በከተማዋ የኮሪደር ልማት ስራ የጎብኚዎች ቁጥር ከመጨመር ባለፈ ጅማን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን እድል እየፈጠረላት መሆኑንም አስረድተዋል።


በከተማዋ በተገነባው የኮሪደር ልማት የጎዳና ላይ ፎቶ የስራ እድል የተፈጠረላቸው የከተማው ወጣቶችም ኮሪደር ልማቱ ገቢ እንደፈጠረላቸውም ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በከተማዋ አደባባዮችና ጎዳናዎች በኮሪደር ልማቱ ላይ የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎችን ፎቶ በማንሳት ገቢ እያገኙ ይገኛሉ።


በከተማዋ ኮሪደር ልማት አማካኝነት በተፈጠረላቸው የስራ እድል ደስተኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በጅማ ከተማ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በዋና ዋና መንገድ ዳር የቡና መሸጫ ቤቶች፣ ፈጣን ምግቦች መሸጫ እና የእንጨት ውጤቶች መሸጫ ሱቆች በብዛት ስራ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026