የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ለገና በዓል የእርድ እንስሳት እና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት ችለናል-ሸማቾች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን ለገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆናቸውን የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በዞኑ በአበሽጌ ወረዳ ዋልጋ ገበያ የእርድ ከብት ሲገዙ ያገኘናቸው አቶ ያለው በለጠ፤ ገበያው ላይ የእርድ ከብቶች በግ፣ ፍየል እና በሬ በበቂ መጠን መቅረቡን ተናግረዋል ።

በዚህም እንደየአቅምና ፍላጎት አማርጦ ለመግዛት የሚያስችል ሁኔታ መፍጠሩን ነው የገለጹት።


እሳቸውም በአቅማቸው ልክ ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለአራት የቅርጫ በሬ መግዛታቸውን ጠቅሰው በዓሉን ከአቅመ ደካሞች ጋር ማዕድ በመጋራት ለማክበር ተዘጋጅተናል ነው ያሉት።

የበሬ ነጋዴ የሆኑት አቶ ጅላሉ ወርቁ፤ በበዓል ገበያው ሸማቹ እንደየአቅሙ ለመሸመት የሚያስችል የእርድ እንስሳት በበቂ ሁኔታ መቅረቡንና ዋጋውም ተመጣጣኝ መሆኑን አንስተዋል ።

አቶ ጅላሉ አክለውም ለግብይት የሚሆን ገንዘብ በኪስ ይዞ ከመንቀሳቀስ ዲጂታል አማራጭ እንደሚጠቀሙ ጠቅሰው ይህም ከስርቆትና መሰል ስጋቶች ይታደጋል ብለዋል ።

አሁን ላይ የዲጂታል ግብይት አማራጭ እየተለመደ መምጣቱ ስራው ላይ እንዲያተኩሩ ማስቻሉን ጠቅሰው በአርሶ አደሩ ዘንድ የሚታየው የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት መሰራት አለበት ብለዋል።

ሌላኛዋ በዞኑ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ መሰለች ዘበርጋ ለበዓሉ ቅመማ ቅመምን ጨምሮ ዶሮ፣ እንቁላል እና ሽንኩርት በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸው በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ ያስችላል ብለዋል።


በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ለበዓሉ የሚሆኑ የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ቀደም ብለው መቅረባቸው ገበያውን የተረጋጋ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ወይዘሪት እፀገነት ተበቃ ናት።

የከተማ አስተዳደሩ ዋጋን ከመቆጣጠርና የምርት አቅርቦት ፍሰት እንዲኖር ለማድረግ የሰጠው ትኩረት ገበያው እንዲረጋጋ ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በዓሉንም አቅመ ደካማ ወገኖችን በመጠየቅ እንሚያሳልፉትም ጠቁመዋል።

በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች በበቂ ሁኔታና በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርበው ግብይት እየተከናወነ መሆኑን የጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ውድማ አረጋግጠዋል ።


በተለይም ምርቶቹ ከደላላና መሰል ጣልቃ ገብነት በጸዳ መልኩ በቀጥታ ለሸማቹ እንዲቀርብ ከአምራቾች ጋር ትስስር መፈጠሩ ገበያውን ማረጋጋቱን ጠቅሰው ሸማቹ የሚፈልገውን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ማስቻሉን አብራርተዋል።

ምርት የሚደብቁ፣ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉና ባዕድ ነገሮችን የሚቀላቅሉ አካላትን አሳታፊ በሆነ መልኩ የቁጥጥር ስራ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ታምራት በሁሉም አካባቢዎች የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025