የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ለገና በዓል የእርድ እንስሳት እና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት ችለናል-ሸማቾች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን ለገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆናቸውን የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በዞኑ በአበሽጌ ወረዳ ዋልጋ ገበያ የእርድ ከብት ሲገዙ ያገኘናቸው አቶ ያለው በለጠ፤ ገበያው ላይ የእርድ ከብቶች በግ፣ ፍየል እና በሬ በበቂ መጠን መቅረቡን ተናግረዋል ።

በዚህም እንደየአቅምና ፍላጎት አማርጦ ለመግዛት የሚያስችል ሁኔታ መፍጠሩን ነው የገለጹት።


እሳቸውም በአቅማቸው ልክ ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለአራት የቅርጫ በሬ መግዛታቸውን ጠቅሰው በዓሉን ከአቅመ ደካሞች ጋር ማዕድ በመጋራት ለማክበር ተዘጋጅተናል ነው ያሉት።

የበሬ ነጋዴ የሆኑት አቶ ጅላሉ ወርቁ፤ በበዓል ገበያው ሸማቹ እንደየአቅሙ ለመሸመት የሚያስችል የእርድ እንስሳት በበቂ ሁኔታ መቅረቡንና ዋጋውም ተመጣጣኝ መሆኑን አንስተዋል ።

አቶ ጅላሉ አክለውም ለግብይት የሚሆን ገንዘብ በኪስ ይዞ ከመንቀሳቀስ ዲጂታል አማራጭ እንደሚጠቀሙ ጠቅሰው ይህም ከስርቆትና መሰል ስጋቶች ይታደጋል ብለዋል ።

አሁን ላይ የዲጂታል ግብይት አማራጭ እየተለመደ መምጣቱ ስራው ላይ እንዲያተኩሩ ማስቻሉን ጠቅሰው በአርሶ አደሩ ዘንድ የሚታየው የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት መሰራት አለበት ብለዋል።

ሌላኛዋ በዞኑ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ መሰለች ዘበርጋ ለበዓሉ ቅመማ ቅመምን ጨምሮ ዶሮ፣ እንቁላል እና ሽንኩርት በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸው በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ ያስችላል ብለዋል።


በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ለበዓሉ የሚሆኑ የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ቀደም ብለው መቅረባቸው ገበያውን የተረጋጋ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ወይዘሪት እፀገነት ተበቃ ናት።

የከተማ አስተዳደሩ ዋጋን ከመቆጣጠርና የምርት አቅርቦት ፍሰት እንዲኖር ለማድረግ የሰጠው ትኩረት ገበያው እንዲረጋጋ ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በዓሉንም አቅመ ደካማ ወገኖችን በመጠየቅ እንሚያሳልፉትም ጠቁመዋል።

በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች በበቂ ሁኔታና በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርበው ግብይት እየተከናወነ መሆኑን የጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ውድማ አረጋግጠዋል ።


በተለይም ምርቶቹ ከደላላና መሰል ጣልቃ ገብነት በጸዳ መልኩ በቀጥታ ለሸማቹ እንዲቀርብ ከአምራቾች ጋር ትስስር መፈጠሩ ገበያውን ማረጋጋቱን ጠቅሰው ሸማቹ የሚፈልገውን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ማስቻሉን አብራርተዋል።

ምርት የሚደብቁ፣ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉና ባዕድ ነገሮችን የሚቀላቅሉ አካላትን አሳታፊ በሆነ መልኩ የቁጥጥር ስራ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ታምራት በሁሉም አካባቢዎች የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026